Friday, February 27, 2015

አድዋ-የጥቁር ህዝቦች ኩራት

ዝክረ ዓድዋ  (የዓድዋው ሰማዕት! የአምባላጌው ጀግና!! የጦር አበጋዙ ፊታውራሪ ገበየሁ አባ ጎራ)
የንጉሰ ነገስቱ የመሀል ጦር አዛዥ ፊታውራሪ ገበየሁ ከጣልያኖች ጋር በተደረገው በሁሉም ጦርነት የተመሰከረላቸው ጀግና ነበሩ። የአምባላጌውን ምሽግ በመስበር በጣልያን ላይ የመጀመሪያውን የድል ደወል ያሰሙት እና ዋናው የድሉ ባለቤት እርሳቸው ነበሩ። በዚህም ምክንያት በወቅቱ የፈረንሳይ ጋዜጦች “የአምባላጌው የኢትዮጵያ ጀግና” በማለት እንዳወደሷቸው ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ ፅፈዋል። የመቀሌውንም ጦርነት በደንብ ተካፍለው በጀግንነት ሲዋጉ እጃቸውን የቆሰሉ ሲሆን ከጦርነቱ በፊትም ራስ መኮነን የዕርቅ ነገር በሚነጋገሩበት ጊዜ ገበየሁ እየተዋጉ ስለ አስቸገሩ እንደ አምባላጌው እንዳይዋጉ አስረዋቸው ሳለ በኋላ ግን ላይዋጉ አስምለው አስለቀቋቸው።
በኢትዮጵያም ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከሁሉም የላቀው የአድዋ ጦርነት የተጀመረው በየካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ከማለዳው ላይ ነበር።

Wednesday, February 25, 2015

ጀግናው አርበኛ በላይ ዘለቀ (አባ ኮስትር) ክፍል -1



በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ
ዘለቀ ላቀው (የበላይ ዘለቀ አባት) የልጅ እያሱ አንጋች ነበሩ ልጅ እያሱ ሲገለበጡ ዘለቀ ላቀው ወደሚስታቸው አገር ወደ ጫቀታ ሄደው ልጆቻቸውን ይዘው ወደአገራቸው ወደ ለምጨን (ቢቸና ወረዳ ) ተሻገሩ (ቢቸና ጎጃም ውስጥ ጫቀታ ወሎ ውስጥ ከአባይ ወንዝ ማዶ ለማዶ ናቸው ይገበያያሉም ይጋባሉም
1916 .. ማለት በላይ ዘለቀ 14 አመት ልጅ ሳለ ፊታውራሪ እምቢ አለ የተባለ የራስ ሀይሉ ሌባ አዳኝ (ጸጥታ አስከባሪ ) ዘለቀ ላቀውን ከበባቸው ዘለቀ ላቀው እጄን አልሰጥም ስላሉ ተኩስ ተከፈተ ዘለቀ ላቀውና አብረዋቸው የነበረ አለሙ መርሻ የተባሉ ወንድማቸው ከአስ ሰው በላይ ገድለው ብዙ ሰው አቆሰሉ «እኛ ልጆች ተኩስ ካባራ በህዋላ ተየጫካው ስንመለስ ሁለቱም ሞተዋል የዘለቀ ላቀው ሬሳ እበቱ በራፍ ላይ ተሰቅሎዋል » አሉ ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ እንግዲህ በላይ ዘለቀና ተሻለ አለሙ እኩል አባቶቻቸውን አጡ አብረው የሀዘንን ጽዋ ቀመሱ እኩል በቀልን እያሰላሰሉ አደጉ በሁዋላም አብረው ጠላትን ተዋጉ

ዘለቀ ላቀው ሲሞቱ ልጆቻቸው ወደእናታቸው አገር ወደ ጫቀታ ተመለሱ በላይ ዘለቀ ያባቱን ደም ለመመለስ ተኩስ እየተማረ አደገ አደገና ያባቱን «ናስ ማሰር» (ባለ ነሐስ ማሰርያ ) ውጅግራ ጠመንጃ ይዞ ወደ አባቱ አገር ወደ ለምጨን (ቢቸና )ተሻገረ ። አባቶቻቸው የተገደሉባቸው ጎረምሶች ዳኝነት እንዳይሹ ዳኛው ራስ ሀይሉ ሆኑባቸው የቀራቸው ምርጫ በቀል ነው ። መሳርያ እየገዙ እየተዘጋጁ ለምጨን ቀንጦ ማርያም እያረሱ ቀን ይጠብቁ ጀመር ...እንዲህ ሲል ጥልያን መጣ ...

Friday, February 13, 2015

የብሪታንያ ፓርላማና አከራካሪው የጽንስ ምርምር (የስልጣኔ ዕብደት)

የብሪታንያ ፤ የሕዝብ እንደራሴዎች ፣እ.አ.አ የካቲት 4፣ 2015 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ፣ በአዲስ የሥነ ተዋልዶ ሥነ ቴክኒክ በመታገዝ ፣ አንድ ሕጻን ከሦስት ግለሰቦች ፤ ማለትም ከእናትና አባት ሌላ የአንዲት ሌላ ሴት ዘረ መል እንዲወርስ ማድረግ የሚቻልበትን ሁኔታ ፤ በድምፅ ብልጫ ፤ በሕግ መምሪያው ም/ቤት 


በኩል ተቀባይነት ለማግኘት በቅቷል። በፓርላማው ክርክር ከተካኼደ በኋላ ፣ 382 የሕዝብ እንደራሴዎች የተጠቀሰው ሥነ ቴክኒክ ሥራ ላይ እንዲውል ሲደግፉ 178 ተቃውመዋል። በሚመጡት ሳምንታት የሕግ መወሰኛው ም/ቤት በተመሳሳይ ሁኔታ በድምፅ ብልጫ ከደገፈው በሕግ ይጸድቃል ማለት ነው።
የብሪታኒያ ፓርላማ ሕጉን በድምፅ ብልጫ የተቀበለው በሰፊው ከተከራከረበት በኋላ ነበር ።ከወግ አጥባቂው ፓርቲ የፓርላማ አባልና ምክትል የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ጄይን ኤልሰን (Jayne Elison)