Thursday, September 29, 2016

ሁሌ_ጥቁር_መርዶ...

" ቀይ ባህር ማዶ~እሺ ሰው ሰመጠ
በሳውዲ አደባባይ~አንገት ተቆረጠ
በሰሜን ደቡብ~እልፍ ሰው ታሰረ
መሪና ተመሪ~ሁሉም አመረረ፤
አምሳ ተገደለ
እቤት ተቃጠለ"
.
.
ነው መሪ ዜናችን~ አገር ቤት ከማዶ
ሰላም ማውራት ቀረ~ሁሌ ጥቁር መርዶ፤

"ትንሽ ስጋ ይዞ ወደ በሬ ጠጋ…"

                                           (የሌቦች ጥበብ)
የሆነ ቦታ ነኝ-ከ ኦሮሚያ ሰማይ ስር፡፡ ትዕቢት የሚባል ምግብ 1-5 ተደራጅተን እየበላን ነው፡፡ ……(ለምን ትዕቢት የሚል ስያሜ እንደተሰጠው ግን የሚያውቅ የለም……ምን አልባት ይህን ምግብ የፈለሰፈው “ትዕቢት” የሚባል ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ ምን አልባትም “ትእቢተኛ” ሰው ሊሆን ይችላል፡፡) ከመሃከላችን በቅርቡ የተሾመ የአንድ ትልቅ ተቋም ሀላፊ አለ፡፡ በተቋሙ ስለነበረው ስር የሰደደ የሙስና መረብ ማውራት ጀመረ፡፡ መረቡን ለመበጠስ እየሞከረ እንደሆነም ነገረን፡፡….ግን ብዙ ውሾች እየጮሁ እንዳስቸገሩትም ነገረን፡፡ …..የትኞቹ ውሾች? ለምን ጮሁ? ብለን ጠየቅነው፡፡
 “ነገር በምሳሌ ጠጅ በብርሌ”…… እንዲሉ በምሳሌ ሊያስረዳን…… “ነገሩ አንዲህ ነው” ሲል ጀመረ፡ 
 “……..አንድ የጥንት የበሬ ሌቦች ጥበብ አለ፡፡ ሌቦቹ በሌሊት ከመንጋው መሃል በሬዎችን ለይተው ለማውጣት ሲሄዱ ከ ቀራተኛው በ ከፋ መልኩ ፈተና የሚሆኑባቸው ውሾች ናቸው፡፡ ስለዚህ የእነሱን ጩኸትና ልፊያ ለማለፍ ሲሉ ትንሽ ቁርጥራጭ  ስጋ ለውሾች ይዘው ይሄዳሉ፡፡ መጮህ ሲጀምሩ ትንሽ ስጋ ጣል ያደርጉላቸዋል፡፡ አሁንም ሲጮሁ ትንሽ ስጋ ጣል ያደርጉላቸዋል፡፡ አንደኛው ሌባ ውሾችን ሲያታልል አንደኛው በሬውን ይፈታል፡፡ ውሾችም በተደጋጋሚ ቁርጥራጭ ስጋ የሰጣቸውን ሰው እየተላመዱ ይሄዱና መጮህ ያቆማሉ፡፡ በቁርጥራጭ ስጋ ልሳናቸው ተዘግቶ የ ጌታቸውን በሬ ከመንጋው ለይተው ይዘው ሲሄዱ ዝም ይላሉ፡፡ በትንሽ ስጋ ብዙ ስጋ የያዘውን በሬ አሳልፈው ይሰጣሉ፡፡ አንድ ቀን ጌታቸው ይህን በሬ አርዶ ከዚህ በላይ ስጋ እንደሚያበላቸው ለ አፍታ ማሰብ አይችሉም፡፡ ጊዜያዊ ጉምጅታው በ አደራነት የሚጠብቁትን ታላቁን በሬ አሳልፈው እንዲሰጡ ያርጋቸዋል፡፡ ከዚህም አልፎ ሌባውን እንደጌታቸው ይቀርቡታል፡፡ …..” ሲል አስረዳን፡፡

Monday, September 12, 2016

የ 2009_አብይ_መልዕክት

#በታደሰ_ቁጥር_የምንቀር_ከኋላው
       (
በውቀቱ ስዩም)
አንድ እግሬን 2008 ላይ ተክዬ፣ አንድ አግሬን ደግሞ ወደ 2009 ለማራመድ ድንበር ላይ ቆሜአለሁ፡፡ የዘመን ድንበር ላይ! ማቆም አይደለም አይን ጥቅሻ ማዘግየት የማንችለው የዘመን ድንበር ላይ! እንደ ዘንድሮ አዲስ ዓመት ግራ አጋብቶኝ አያውቅም፡፡
ይህን የምለው በዓሉ ድምቀት ሳይሆን ከልቤ ነው፡፡ ……..ሰው የተሻለ ነገር ሲናፍቅ አዲስ አመትን አይደለም ነገ መንጋት በጉጉት ይጠብቃል፡፡
.......
ልጅነቴ ዘመን መለወጫ ቀን የሚሰጠኝን አዲስ እጀጠባብ (ካሽመር ሙሉ ልብስ) በማሰብ የጳጉሜን ሌሊቶች ሙሉ እንቅልፍ አይወስደኝም ነበር፡፡ አሁን ግን በመኖር እንጂ ካሽመር የሚታለል ልብ የለኝም፡፡