Friday, September 22, 2017

የጋሽ በጋሻው ነገር!

‹‹ ሳይማር ያስተማረና ሳይተርፈው የደገሰ ትርፉ ፀፀት ነው››
                    መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ
ሰሞኑን የማህበራዊ ሚዲያዎች ‹‹ጋሽ በጋሻው ለምዱን ገፎ በገሃድ ኦርቶዶክስ ይደለሁም አለ››…….አንዳንዶች ደግሞ ‹‹እምነት የለኝም አለ›› ሌሎች ደግሞ ‹‹ፕሮቴስታንት ነኝ አለ›› ይላሉ፡፡ ነገ ደግሞ ይህ ሰውዬ ‹‹ሰው አይደለሁም›› ብሎ እንዳይመጣ እፈራለሁ፡፡
አንድ ሰው የየትኛውም እምነትና ሐይማኖት (ሁለቱ የተለያዩ ናቸው) አማኝና ተከታይ ከመሆኑ በፊት ሰው መሆን አለበት፡፡ አንድ ሰው ‹‹ሰውነት›› ከተላበሰ ያውም በሐይማኖት ስም ለብዙዎች መሰናከያና መወናበጃ ምክንያት መሆን የለበትም፡፡ የሚያምንበትን ነገር ከስር መሰረቱ ግልፅ አድርጎ የፈለገውን ሃይማኖት መከተል መብቱ ነው፡፡ በሌሎች ጓዳ እየገቡ መፈትፈት ግን ኢሞራላዊ ነው፡፡

Wednesday, September 13, 2017

ዘመን ሲታወስ-መስከረም 2፣ 1967 ዓ.ም

(ኢትዮጵያ ትቅደም ያለምንም ደም)

ወደ ኋላ 43 ድፍን ዓመታትን እንደ ንስር በረን መስከረም 2 1967 .ምን እናስባት፡፡ ይች ቀን ታሪካዊ ቀን ናት-ያለምንም ደም ስልጣን አፄው ወደ ወታደራዊው መንግስት የተላለፈባት ቀን፡፡ ጅምሩ ተራማጅ ኃይሉን እየመሩ ከፍተኛ ተቀባይነትን እያገኙ በመጡት በአልጋወራሽ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ፣ ኢትዮጵያ በአፄ ሚኒሊክ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የስልጣኔ እርምጃዎችን መራመድ ጀመረች፡፡

Saturday, September 9, 2017

መልካም አዲስ ዓመት (2010 ዓ.ም)

1)    http://zelalemtilahun.blogspot.com/ የምትከታተሉኝ 132,000 በላይ ሰዎች
2)    https://www.facebook.com/zelalem.tilahun.12 ጓደኝነታችሁን ያጋራችሁኝ 6,257 ሰዎች
3)     https://www.facebook.com/WegagiraUniversity/ ገፄን Like ያረጋችሁ 9,852 ሰዎች
4)     https://www.facebook.com/-እሳት-ዳር-ተረቶች183819932149086/ የምትከታተሉ 3,022 ሰዎች

5)     https://www.facebook.com/groups/1018394138191997/ የግጥም ፀሐዮች አባል የሆናችሁ 18, 223 ሰዎች በሙሉ:
እነሆ ከልብ  የመነጨ የአዲስ ዓመት ምኞቴ ይድረሳችሁ !
መልካም አዲስ ዓመት !

===2010
.===

Wednesday, September 6, 2017

የአያ ሙሌ ነገር!

የአያ ሙሌ ነገር ግራ ነው! ሕይወቱም ሲበዛ ዥንጉርጉር ናት፡፡
ለምሳሌ ተራ ገጣሚ ነው እንዳንል እጅግ ተወዳጆቹ ሙዚቃዎች የርሱ አሻራ ያረፈባቸው ኾነው እናገኛለን፡፡ ብኩን ሰው ነው እንዳንል በኢህአፓ እሳት ፖለቲካ ዉስጥ ተወልዶ፣ በማርክሲዝም ሌኒኒዝም ነዶ፣ በብአዴን በስሎ፣ NGO ደመወዝ ከብሮ፣ በኢህአዴግ ላዕላይ ቤት ገብቶ፣ በጋዜጠኝነት ሠርቶ፣ ከመንግሥት አፓርታማ ተበርክቶለት የሴኮ ቱሬ ጎረቤት ኾኖ የኖረ ሰው ነው፡፡
ደግሞ ያን ሰምተን ለአንቱታ ስናዘጋጀው ድንገት ሥራውን ጥሎ ይጠፋል፡፡ ዘበኛ፣ ኩሊ፣ ወዛደር፣ ጎዳና ተዳዳሪ ይሆናል፡፡ ብቻ ያያ ሙሌ ነገር ለወሬም አይመች፡፡