Tuesday, October 31, 2017

ኢትዮጵያ ማለት………

(ከታዋቂ ሰዎች አንደበት)
‹‹ኢትዮጵያዊነት እንደ እንጉዳይ በአንድ ማታ የበቀለ አይደለም››
‹‹
ኢትዮጵያ ውስጥ የመደብ እንጅ የብሔር ጭቆና ኑሮ አያውቅም››
‹‹
ኢትዮጵያ የአስተሳሰብ ቆሻሻን የማፅዳት ጦርነት የሚያስፈልጋት ሃገር ናት……››
‹‹
ኢትዮጵያዊነት ሁሉን የመሳብ አቅም ያለው ልዩ ሃይል ነው››
‹‹
ገዥው ኢህአዲግ ሁለት ምርኩዝ አለው፡ ጠብ መንጃና ምርጫ ቦርድ››

‹‹ኢትዮጵያዊነት ቢገፉት የማይወድቅ፣ ቢከፍሉት የማይሰነጠቅ፣  በፅኑ ዓለት ላይ ፀድቆ የኖረ፣ በአጥንትና በደም የተሳሰረ ህያዊነት ነው››
ኢትዮጵያ ዘላለም ትኑር!

Tuesday, October 17, 2017

ይወለዳል ገና!

 ይሄ ወጣትነት
ከሱስ ላይ ተጥደን፥ ያልፋል እንደዘበት፤
ይሄ ወጣትነት
ያልፋል እንደ ዋዛ
ለሃብታም ስናረግድ፥ ለውሸት ስንገዛ
ይሄን ወጣትነት
የኔ ቢጤ ሁሉ፥ ይሰዋል በከንቱ
አሸሸገዳሜ፥ ለሚጠፋ አምሮቱ


ጀግናው ተሜ ግን፥ የሀገሬ እንቆቆ
ስለ መራራ እውነት፥ ጣፋጭ ዓለም ንቆ

Saturday, October 7, 2017

ኧረረረረ ወገቤ……................

አንቺ ማንጠግቦሽ አተላውን ቶሎ አምጪው ባክሽ
ምን ይች ልጅ ተጨማሪ ህመም ሆነችብኝሳ!