Monday, November 27, 2017

‹‹አንድም እናት በወሊድ ምክንያት…..››

-----------------------------------
‹‹
ሌሊት ላይ ታመመች
ምጤ መጣ ብላ፣ ሆስፒታል ውስጥ ገባች
አማጠች አማጠች
ሌሊቱ ጎህ ሳይቀድ፣ ሞት ተገላገለች፤
ሁሉም ሰው አዘነ፣ ዘመድ አለቀሰ
ሁለት ነፍስ፣ በአንድ ጉድጓድ፣ ቀብሮ ተመለሰ››
በቃ!

--------------------------------------------
ይህ ዜና በጓደኛዬ እህት ደርሶ ሐዘኑ ምን ያህል ልብ ሰባሪ መሆኑን በአይኔ ልመልከት እንጂ የብዙ ኢትዮጵያውያንን ቅስም ለዘመናት ሲሰብር የኖረ ሰቆቃ ነው፡፡ የነፍሰጡር ሞት አንድ ሞት አይደለም፣ የብዙ ሞቶች ጥርቅም ነው፡፡