Sunday, February 25, 2018

የጠቅላዮች ምረጡኝ ቅስቀሳ

የጠቅላዮች ምረጡኝ ቅስቀሳ (ምረጧቸው ቅስቀሳ) ተጧጡፏል፡፡ የ<ለማ>ንና የ <ዶ/ር አብይ>ን 'ሲንግል' ዘፈኖች አደመጥሁ፡፡ ዘፈኖቹ ‹‹ሃሳብ አለው ለማ›› እና ‹‹አብይ ዜማ›› ይሰኛሉ፡፡  የ<ደመቀ> እና የ <ሲራጅ> ይቀረኛል፡፡ ያደመጣችሁ ጀባ በሉኝ፡፡ ዘፈን ለመስራት ያሰባችሁ ደግሞ ግጥሙን ከአዝማሪ፥ ዜማውን ከህዝብ አጣምሩና በቶሎ በሉ፡፡ በእርግጥ ደህዴንና ህዋሃት ያየር ሰዓቱን በዝረራ ያስረከቡ ይመስላል፡፡ እንቅስቃሴው ደከም ያለ ነው፡፡

አጋር ድርጅቶች ደግሞ እስከ ብብት እንጂ ጭንቅላት ድረስ መውጣት አልተፈቀደላቸውም፡፡ ጠ/ሚንስትር መሆን የሚፈልግ ባለምጡቅ ጭንቅላት ሶማሊያዊ፥ አዳል ወይም ጋምቤላዊ መጀመሪያ የዘር ካርዱን ከትግሬ፥ ከኦሮሞ ወይም ከአማራ የደም ማህተም ማስመታት ይኖርበታል፡፡ ይች ናት እንግዲ-የብሔር እኩልነት የነገሰባት ሀገር!
ጭንቅላት ብቻውን ጭንቀት ከመፍጠር ያለፈ ዋጋ የለውም፡፡
<<የሀገሬ ዳቦና፣ የዘር ፖተሊካ
ለአንዳንዱ ባካፋ፣ ለአንዳንዱ በሹካ>> አይነት ነገር ነው፡፡ ለማንኛውም፥ ኢህአዲግዬ የመጨረሻውን ጥይት ለመተኮስ የተዘጋጀ ይመስለኛል፡፡ ዶ/ር አብይ አህመድን!
ቀሪውን፥ ቀሪው ቀን ያውቃል!!!

Thursday, February 15, 2018

Ethiopian Prime Minister Resigned

The current Ethiopian Prime minster and EPDRF Leader, Hailemariam Desalegn resigned from his position 
የኢትዮጵያ መራሒ መንግስት ክቡር ሐይለማርያም ደሳለኝ ‹‹በሰለጠነ መንገድ›› መልቀቂያ አቅርበዋል-እሳቸው እንዳሉት፡፡ የእራሳቸውንም መልቀቅ አሁን ላለው የኢትዮጵያ ሁኔታ የመፍትሄ አካል አድርገው አቅርበዋል፡፡ እሳቸው እንዳሉት በታሪክ ስልጣኑን በፈቃዱ የለቀቀ ሰው ተብዬ እታወሳለሁ ብለዋል፡፡ ነገር ግን ትልቁ የህዝቡ ጥያቄ ከስርዓቱ ወይስ ከሐይለማርያም? የሐይለማርያም መልቀቅ አንድ እርምጃ ወደፊት ያስኬዳል ወይ?

ነገሮች መልካቸውን እየቀየሩ ሄዱ፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል ሀገር ታሳዝናለች፡፡ ይች ሀገር የምታሳዝነኝ ግን ‹‹መንቀል እንጂ ማብቀል›› የሚችል ማህበረሰብ መፍጠር አለመቻላችን ነው፡፡ ሁሉም ሰው ‹‹ወደ ገደል መጎተቱ ላይ እንጂ››፣ ጎን ለጎን ‹‹ወደ ተራራው የሚወጡትን›› የመግፋት ነገር ላይ ሲሰራ አይታይም፡፡  ዛሬ እየፈረሰ መሆኑን ከተረዳን ነገን መስራት ላይ ማሰብና መዘጋጀት ያስልጋል፡፡