Wednesday, September 12, 2018

ሀሳብና ሰብዕና ቢለያዩስ?


/ መስፍን ወልደማሪያም ለኢትዮጵያ ውለታ ከዋሉ አንጋፋ ምሁራን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ከአፄው እስከ አሁኑ ስርዓት ድረስ የታሪክ ማጣቀሻ ሆነው በህይወት ካሉ ምሁራን ውስጥ አንዱ እኒህ ጎምቱ የታሪክ ምሁር ናቸው፡፡ 1960ዎች ኢትዮጵያ በረሃብ አለንጋ ስትገረፍ ከፕ/ ጌታቸው ኃይሌ እና መሰል የወገን ተቆርቋሪዎች ጋር በመሆን ታላቅ ውለታ ውለዋል፡፡ እኒህ ምሁር ‹‹አማራ የሚባል ብሔር/ ነገድ የለም›› በሚል አቋማቸው አማራ ነህ ተብሎ እንደ ኑግ በየቦታው እየተሰለቀ በነበረው ወጣት ዘንድ ትልቅ ተቃውሞ ሲሰነዘርባቸው እንደቆዬ ሁላችንም የምናውቀው ነው፡፡ የአሁኑ ዘመን ትውልድ ከእሳቸው አቋም ጋር መስማማት ቢሳነው በማንም መፍረድ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም በእሳቸው ትርክት እና በእኛ ትርክት መካከል ትልቅ የታሪክ መጋረጃ አለ፡፡ የታሪክ መጋረጃው ደግሞ ሰው በሰውነቱ ሳይሆን የደምና የአጥንቱን መሰረት ተከትሎ በዘውጌ ፖለቲካ እንዲተሳሰር ተደርጎ የተዘጋጀ መጥፎ መጋረጃ ነው፡፡ / መስፍን በሀሳባቸው ልክ ሆኑም አልሆኑም፣ ሰብዕናቸው መከበር አለበት፡፡ 

Monday, September 10, 2018

‹‹በደሃ እናቶች እምባና በወጣቶች ደም-የስልጣን ቁማር መጫወት ይብቃ!››

(የአዲስ ዓመት መልዕክት)
 
የፕ/ ብርሃኑ እናት ልጃቸውን ቦሌ ተቀብለው ለመሳም ታደሉ፣ የሌሎችም እንዲሁ፡፡ ያም ሆኖ ግን ስስታቸውን ምስሉ ይገልፀዋል፡፡ እናት ምንም ቢሆን እናት ናት፡፡ ለሴኮንድም የልጇን መከራ መስማት አትፈልግም፡፡ ከጀርባ ግን ታላቅ የእምባ ጎርፍ ይታየኛል፡፡ ልጆቻቸውን በአደባባይ በአገዛዙ በግፍ የተነጠቁ እናቶች፣ መሰል ምስሎችን ሲያዩ የሚያነቡት እምባ!  ከአንጀት ተንሰቅስቆ የሚወርድ ትኩስ አምባ! በበቃሽ የማይቆም እምባ!