Wednesday, October 17, 2018

"ቆፍቁፍን ሰድጄ፥ ሸርድምን አመጣሁ"

አባቴ ከሚያውቀው የባሰ ነገር ወይም የባሰ ወዳጅ ሲገጥመው "ቆፍቁፍን ሰድጄ ሸርድምን አመጣሁ" ይተርታል፡፡ ተረቱ እንዲህ ነው፡
"አንድ ሰው ነበር፡፡ ሚስቱ በየቀኑ ለከብቶች ብሎ የገዛውን አሞሌ ጨው እየቆፈቆፈች ትፈረካክስና ለምግብ መስሪያ ትጠቀማለች፡፡ ባል ተቆጣና ፈታት፡፡ ሌላ ሚስት አገባ፡፡ ይችኛዋ ሚስት የበፊቱን የፍች ታሪክ ታውቅ ነበርና አሞሌ ጨውን በመቆፍቆፍ መፈረካከስ አልፈለገችም፡፡ ፍች ሊያመጣባት ይችላል፡፡ ስለዚህ የተሻለው አማራጭ ድምፅ ሳታሰማ በጥርሷ መሸርደም ነው፡፡ አደረገችው፡፡ Just she was a "silent killer". ባል ብዙ ቀን ከተሞኘ በኋላ አንድ ቀን እውነቱን አወቀ፡፡ ከዚያም ሰዎች አንድ ቀን አዲሷ ባለቤትህ እንዴት ናት አሉት? ኧረ ተውኝ "ቆፍቁፍን ሰድጄ ሸርድምን አመጣው" አለ ይባላል፡፡
ምን ማለት እንደፈለግሁ ይገባችኋል ብዬ አስባለሁ፡፡ ካልገባችሁ አሞሌ ጨው ተሸርድሞ ሲያልቅ ይገባችኋል፡፡