Thursday, July 23, 2015

በመጥረጊያ

                             (ፀሐፊ፡ ጦቢያ ዓለም): Tobyaalem@gamil.com
እኔ ጦቢያ ተነሳሁ! አለከልካለሁ፡፡ ድክም ብሎኛል፡፡ የሆነ ዳገት እየወጣሁየሆነ ትልቅ ተራራ ላይ እየዳሁ ያለሁ ይመስለኛል፡፡ ደግሞ በህልም ወይንም በቅዥት ውስጥ ያለሁም ይመስለኛል፡፡ ጉዋደኛየ ይጠራኛል….አቤት…..….ምን?….ከደቂቃዎች በፊት ወደ አንድ 'ጥንት ህክምና ተቋም እንደ ወሰደኝ አስታውሳለሁ፡፡ እንዴውም በጣም የሚያምረውን የተቋሙን ወለለ ስረግጥ አድጦኝ ወድቄ ዲስኬ እንዳይንሸራተት እያልሁ በፍርሀት በጥፍሬ እየቆነጠጥሁ (ደግሞ ጥፍሬ ለጉድ ነው..ለዚህ አጋጣሚ ተብሎ የተሰራ መሰለኝናዝቅ ብየ አየሁት) ደረጃዎቹን እንደ ወጣሁ አልረሳም፡፡ አንተ ጦቢያጦቢያጦቢያ አለም፡፡ አልሰማው ስል የናቴን ሰም ጨመረው፤ አለም፡፡ በጣም ስለምወዳት አሻፈረኝ ብዬ በናቴ ስም ነው የምጠራው፡፡ የናቴ ስም ሲጠራ ሞቼ ራሱ ምነሳ ይመስለኛል፡፡ አቤት ብየ ብድግ አልሁ…….የሆነ ጫጫታ ተሰማኝ፡፡

Wednesday, July 22, 2015

ይድረስ ለባራክ ኦባማ

         Click for PDF
            
ይድረስ፡ ለ ባራክ ሁሴን ኦባማ ንጉሰ ነገስት ዘ አሜሪካ
            ተላከ፡ ከ ወጣት እርቅይሁን በላቸው ዘብሔረ ኢትዮጵያ
ኦቡየ እንዴት ነህ፡፡ አማረኛ ታነባለህ አይደል፡፡ መቼም በየጊዜው “ኋይት ሀውስ” የሚመጡት አበሾች አስጠንተውሃል ብለውኝ ነው፡፡ ሰማሁ ኦቡየ፣ ወሬ አይደበቅም፡፡ በእኛ ሀገር “ወሬን ተራራ አይጋርደውም” ተብሎ ይተረታል፡፡ በእናንተስ ኦቡየ ወሬን ፎቅ ምናምነ አይጋርደውም ትላላችሁ፡፡ እንዴው ለነገሩ እንጂ እናንተን ምንም አይጋርዳችሁ፡፡ እድሜ ለእነ….ይቀር ተወው፡፡ የራሳችንን ጉዳይ እንኳ እናንተ አላምጣችሁ ከተፋችሁት በኋላ ነው እኛ የምንሰማው፡፡ ኧረ ላንሰማም እንችላለን፡፡ ማለቴ ቴሌና መብራት ትንሽ አመም አድርጓቸው ከዋለ ካደረ ማለቴ ነው፡፡ ለመሆኑ ኢንተርኔት፣ ቴሌ፣ መብራት አሜሪካ እንዴት ነው? ማለቴ…. ይቅርታ ኦቡየ ገና በመግቢያ በነገር አደከምኩህ፡፡ አንተ ግን እንዴት ነህ፡፡ አቦ እናትህም አባትህም እንኳን ወለዱህ፡፡ ይህን 7 ቢሊዮን የዓለም ህዝብ ስምህን አስጠራኸው እኮ፣ ማለቴ ህፃናትም ሲያድጉ አንተን መጥራታቸው አይቀርም ብዬ ነው፡፡ በተለይ አፍሪካ! የአንተ መምጣት እኮ አንደ ምፃት ቀን፣ እንደ መሲህ ምናምን ነው እየታየ ያለው፡፡ አቦ ናልን አሜሪካዊው የዓለም መሲህ! እንኳን ወደዚች ታሪካዊ፣ የተቀደሰችና እንግዳ ተቀባይ ወደ ሆነች አገራችን በሰላም መጣህ፡፡ 

Wednesday, July 15, 2015

“ አንድ ሰው ለአንድ ወገን! ”

Click here for PDF
       (ወገን አልባ ወገኖች)
ፒያሳ ሐምሌ 82007 . ማለዳ 300 ሰዓት፡፡ ፒያሳ ከፀሐይ በተለቀቁት ጨረሮች ፈካ ለማለት እየሞከረች ነው፡፡ ሰው የማያጣት ፒያሳ በሰው ትርመሰመሳለች፡፡ ወደ አስኮ፣ አውቶብስ ተራ፣ አራት ኪሎ፣ ካዛንቺስ መገናኛ ፣ስድሰት ኪሎ፣ ሽሮሜዳ፣ አዲሱ ገባያ ለመሄድ በሚርመሰመስ ሰው፡፡ መሃል ፒያሳ ከወደ አውቶብስ መያዣ አካባቢ አውቶብስ ጠባቂዎች የሚያርፉበት መቀመጫ እንደድሮው አውቶብስ በሚጠብቁ ሰዎች አልተያዘም፡፡ በምትኩ በቤት አልባ ብላቴናዎች ተጨናንቋል፡፡ ቀኑ ሐሩሩና ረሃቡ፣ ሌሊት ደግሞ ቁሩ የተፈራረቀባቸው ብላቴናዎች በጥዋቷ ፀሐይ ሙቀት እንቅልፍ አሸልቧቸዋል፡፡ አንዲት ቤት አልባ የሆነች ውሻም ከቤት አልባ ብላቴናዎች ጋር ጉርብትናን ፈጥራ አብራ ተኝታለች፡፡ ለብላቴናዎች ሙቀትንና ፍቅርን ትለግሳለች፡፡ እነሱም በአጠፋው ፍቅርንና ሙቀትን ብቻ ሳይሆን ከሚበሉትም ያጋሯታል፡፡ ውሻዋ ለብላቴናዎች ምግብ ማጋራቷን ግን እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ነገር ግን በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ውሻና ሰው ተጋርቶ አንድ ላይ ሲበላ ማየት የተለመደ ነው፡፡ በእርግጥ የዚችን ውሻ ያክል ፍቅር እንኳ ማን ሰጣቸው፡፡ ከውሻ የባስን መሆናችንን ሳስበው ዘገነነኝ፡፡

Monday, July 13, 2015

“ጠብሰው አንገረገቡኝ”








(ከአባቴ ተረቶች-፩)፡ ተረት ተረት...
በአንድ ወቅት አንድ ባልና ሚስት አንዲት ትንሽ የገጠር መንደር ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ ባል ሁልጊዜም ራቅ ካለ ቦታ ስንቅ ቋጥሮ፣ ውሃ በኮዳ አንጠልጥሎ ጥዋት ለእርሻ የወጣ ማታ ይመለሳል፡፡ሚስት ከቤቱ ስራ በተጨማሪ አንዳንድ ጊዜ ባልንም በጉልጓሎና በአረም ታግዛለች፡፡ ባል ብዙ ጊዜ  በስራና በመንገዱ እርቀት ደክሞት ይመጣል፡፡ በዚህም ምክንያት የወንድነት ስራውን መዘንጋት ጀመረ፡፡ በዚህ ክፍተት ስሜቷን ለባል መናገር ያፈረች ሚስት ቤት ለቤት ሲያውደለድል የሚውል አንድ ወስላታ የሰፈር ሰው አሽኮረመመችና ወሸመች (ጠበሰች)፡፡ ውሽምየ የባልን ወደ ስራ መሄድ ሰልሎ ቤት ይመጣና ሲያስደግስ ይውላል፡፡ የልቧንም አድርሷት ይሄዳል፡፡ ምስኪን ባል ከውሽምየ የተረፈውን ቀማምሶ እንደለመደበት ድብን ብሎ ይተኛል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሚስት ለባል ያላት ፍቅር እየቀነሰና የሚዘጋጅለት ምግብም በአይነትና በመጠን እየወረደ ሲመጣ ባልዬም መጠርጠር ጀመረ፡፡ ጎረቤት መጠየቅ አልፈለገም፡፡ እራሱ አንድ ቀን በአሳቻ ለመያዝ አሰበ፡፡

Friday, July 10, 2015

ህሊና ብቻ ነው!

ጥላቻ ከፍቅር
መኖር ካለመኖር
ፅድቅና ኩነኔ
ፍርሀትና ወኔ
እውነትና ሐሰት
መውደድና መጥላት
ጤና ከበሽታ
ሀዘን ከደስታ
መማር ካለመማር
እብደትም ከስካር፤
 ተቀላቅለውብኝ
ድንበሩ ጠፍቶብኝ

Monday, July 6, 2015

ግብረ ሰዶም ወ አሜሪካ



የሰዶምና ገሞራ የጥጋብ ኃጢያት፣ የምዕራባውያን የስልጣኔ ዝቅጠት፣ የዓለማችን ታላቁ የተፈጥሮ ክህደት የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ሌዝቢያን፣ ጋይ፣ ባይሴክሽዋል እና ትራንስጀንደር” (LGBT)፡፡ እነሆ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ .. ሰኔ 29 2015 ግብረሰዶምን የሚፈቅድ አዋጅ በይፋ በሁሉም የአሜሪካ ግዛቶች ማፅደቃቸውን ተከትሎ ምዕራባውያን የደስታ ሲቃ ተናንቋቸው ሰንብቷል፡፡1 ናይጀሪያን በመሳሰሉ አንዳንድ የአፍሪካ አገሮች የሚገኙ ዜጎችም ይህንን ዜና ወደ ሀገራቸው ማስተጋባት ጀምረዋል፡፡ በሌላ በኩል የዙምባቡዌው ፕሬዘዳንት ሮበርት ሙጋቤ ግብረሰዶምን በመቃወም ከምዕራባውያን ጋር ቀዝቃዛ ጦርነት ከፍተው የዓለም መነጋገሪያ ሁነው ሰንብተዋል፡፡ በአገራችን ኢትዮጵያም ደስታውን መስቀል አደባባይ ወጦ የገለጠ ወራዳ ባይኖረም በማህበራዊ ሚዲያ አደባባይ ግን ኢትዮጵያዊና ሀበሻዊ ባልሆነ ቃና ይህንን እርኩስ ተግባር ደግፈው የውስጣቸውን የተነፈሱ አልጠፉም፡፡

Thursday, July 2, 2015

የመምህራን ቀልዶችና ምሳሌዎች

መምህራን አንዳንዴ ተማሪ ለጠየቀው ጥያቄ መልስ መስጠት ሲያቅታቸው ወይም ሲደብራቸው ቀልድ አዘል የሆነ መልስ ይመልሳሉ፡፡
ቀልድ አንድ፡ እስኪ አንደኛ ደረጃ /ቤት የሂሳብ መምህር ከነበሩትና ተማሪው ትዕቢተኛ ናቸው ከሚላቸው ከጋሽ _______እንጀምር፡፡
ተማሪ ጋሸ
መምህር አቤት
ተማሪ የሜትርና የኪሎ ሜትር ዝምድናቸው ምንድን ነው፡፡
መምህር አታውቀውም እንዴ፣ የአክስትና የአጎት ልጆች ናቸው፡፡