(ከ ፕሮፌሰሩ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ)
ቢሾፍቱ ነፍስን የሚገዙ ትንንሽ ሀይቆችን በተፈጥሮ የተቸረች ምርጥ ከተማ ናት፡፡ በተደጋጋሚ ጎብኝቻታለሁ፡፡
ግን አልጠግባትም፡፡ ሐይቆቿ ነፍሴን ይገዙታል፡፡ ከ እራሴ ጋር እንዳወራ እድል ይሰጡኛል፡፡ ከ ዓለም ጫጫታ ወጥቼ ከ ማዕበሉ ጉዞ
ጋር ነፍሴን አስማምቼ በምናብ እንድመጥቅ፣ ከ ሀሳቤ ህመሜ ለ አፍታም ቢሆን እንድላቀቅ ይረዱኛል፡፡ ሐይቅ እወዳለሁ፡፡ ጣና፣ ደብረዘይት፣
ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ ዘንገና፣ አለማያ……በተጋጋሚ ባያቸውም አልጠግባቸውም፡፡ ሁሌም ከጉያቸው ቁጭ ብዬ የሚተነፍሱትን አየር ወደ ውስጤ
መማግ ያረካኛል፡፡ ንፁህ አየራቸውን ስስብ፣ አዲስ ተስፋና አዲስ ህይወት ይታየኛል፡፡ ከ ጀርባዬ ያለ ሸክም የተራገፈ ያክል ነፃነት ይሰማኛል፡፡ ጥሎብኝ ሐይቅ ብቻ ሳይሆን ተፈጥሮን
አደንቃለሁ፡፡
ከ ቢሾፍቱ ፈርጦች ውስጥ በ ርዕሰ ከተማዋ ስም የተሰየመችው ቢሾፍቱ
ሐይቅ አፋፍ ላይ ቁጭ ብዬ ከማዕበሉ ጋር በመጫወት ላይ ሳለሁ እርዳታዬን ፈልጎ አንድ አሮጌ ፈረንጂ ወደ ተቀመጥሁበት ወንበር መጣ፡፡
(እዚህ ጋ ያዝ ላድርገውና ስለ ቢሾፍቱ ሐይቅ ትንሽ ልበል፡፡)


