Showing posts with label ግጥም (Poam). Show all posts
Showing posts with label ግጥም (Poam). Show all posts

Tuesday, October 17, 2017

ይወለዳል ገና!

 ይሄ ወጣትነት
ከሱስ ላይ ተጥደን፥ ያልፋል እንደዘበት፤
ይሄ ወጣትነት
ያልፋል እንደ ዋዛ
ለሃብታም ስናረግድ፥ ለውሸት ስንገዛ
ይሄን ወጣትነት
የኔ ቢጤ ሁሉ፥ ይሰዋል በከንቱ
አሸሸገዳሜ፥ ለሚጠፋ አምሮቱ


ጀግናው ተሜ ግን፥ የሀገሬ እንቆቆ
ስለ መራራ እውነት፥ ጣፋጭ ዓለም ንቆ

Monday, July 24, 2017

ይድረስ ለ 'ጃንሆይ'

እንዴት አሉ ጃንሆይ?
ሰላምታ አቅርበናል~ወደ አሉበት ሰማይ
ዓለም ለሚያከብረው~ ክቡር ልደትዎ
ኬኩ ባይቀምሱም~እንኳ አደረሰዎ
እንኳን የእኛ ሆኑ!

………እንኳን ተወለዱ!
ይህን ጭቁን ህዝብ~እንኳ እንደ ላም ነዱ!

Saturday, May 13, 2017

ቃል_አልባ_ስሜቶች

ደብልቅልቅ ሃሳቦች
ቃል አልባ ስሜቶች
እንደ ገጠር ሕፃን በ ጀርባዬ ታዝለው
እንደ ጨቋኝ ገዢ ከ ላዬ ተቀምጠው
ስሄድ ሲመልሱኝ ከ ፊቴ እያለፉ
ስመለስ ሲንጡኝ ከ ኋላ እየገፉ
ወዴት ብዬ ልሂድ ወደ የት ልራመድ
በ ምድር በ ሰማይ በ ታጠረ መንገድ፤

Friday, May 5, 2017

‹‹የ አርበኞቹ ልጆች….››


አያቶቻችን፤
በ ሀገር ፍቅር የሰከሩ
አንበሳ ያሰገሩ
ጥሊያንን የገሩ
ሰንደቋን አንግበው
ረሃብ መከራን ታግሰው
ስለ ወገን  የሞቱ~ድንበር ያስከበሩ
እውነትም ጀግኖች ነበሩ!
እውነትም ፃድቆች ነበሩ!
አባቶቻችን ፤
በ እንጥፍጣፊ ፍቅር
ተዋድቀዋል ለ ሀገር!

Monday, April 24, 2017

ያዳኑሽ_የት_አሉ???

ቤተስኪያን ታዛ~ ካቡ ስር ቆሜ
እግዜሩ አስተብርኮ~ አንቺም ተሳልሜ
ስምሽን እጠራለሁ~ ዜማ ውዳሴ
ደም ስጋሽ ጋር~ተቆራኝታ ነፍሴ፤

እንደምን ዝም ልበል~እንዴት ብዬ ልሽሽ
ሰርክ ያባክነኛል፣ እናቴ ጡጦች ጋር~የጠባሁት ስምሽ
ግን ውዴ፡~

Friday, March 31, 2017

(‹ያለመቻል ግጥም››)

ልፅፍልሽ ብዬ፡
እንደ ገዳም መናኝ ቀልቤን ስሰበስብ
ለ አንቺነትሽ ቅኔ ገላጭ ቃላት ሳስብ
እንደ ርደ-መሬት ትዘላለች ልቤ
ፅሞናዬ ጠፍቶ ይበተናል ቀልቤ
‹‹ ፈዝዤ እቀራለሁ››
ጎንበስ ብሎ መፃፍ ተስኖት ወገቤ

Sunday, March 19, 2017

ለ ዝሆኖች ሲባል…

እዚያ ማዶ
ሰማይ ተዋዶ
የታላቅነት ታሪክ..በታዛቢነት ቆሟል
ትናንት ነገ.. አፉን ከፍቶ ይናገራል!
.
ወዲ ማዶ፡
ትውልድ ግራ ተጋብቶ እግሩ ወደ መራው ያዘግማል
ትናንቱን እየሻረ ዛሬውን ያሞግሳል!
;
መሃል ባለው ገደል
አንዱ አንዱን ሲበድል፤

Tuesday, March 14, 2017

ብርሃን ሩጫ~በሚያልፍ ዘመን ላይ 
እንደ ገለባ እሳት~ ሚከስም ንዋይ
ስነ ሰብዕ በታች~ከማንነት ማዶ
ዛሬነት ግርዶሽ~ነጋችን ተጋርዶ 
ልክ እንደ ይሁዳ~ሰው ገንዘብን ወዶ
.
.
ገዳይ ከሟች ጋራ~ አንድ እያደረ
እንግዲህ ሰው ማመን~እንደ ዋዛ ቀረ
--------------0----------------
      (ዘላለም፡ 29-07-08)

Saturday, February 25, 2017

መ  ነ  መ  ነ  ች   እ  ው  ነ  ት
ብርሀን ደበዘዘ~ጨለማ ደመቀ
ሰው ከሰው ሲቀርብ~ሰው ከእራሱ ራቀ
ማመን መተማመን~ጥለው ተሰደዱ
ፍርሃት ጥርጣሬ~ ልብ ተዋሃዱ፤
አይንና አፍንጫ~ጉርብትና እረሱ
መተዛዘን ቀርቶ~ይሙት ሆነ ክሱ፤
ቅትሎ…. ስቅሎ
ቅትሎ….ስቅሎ
ይላል ግብረ ቃኤል~ክፋት ጀርባ አዝሎ፤

Thursday, February 23, 2017

"አክሚኝ...፩"

አመመኝ
አልችል ስል ተኛሁኝ
.
.
ተኝቼም ሲብሰኝ~በሽታዬ ሲከር
ሄድሁኝ ወደ ሃኪም~ህመሜን ላማክር
.
.
.
ሆስፒታል ገብቼ~ደሜን መረመሩኝ
ትዝታሽ ነበረ~እኔን ያሳመመኝ

Thursday, September 29, 2016

ሁሌ_ጥቁር_መርዶ...

" ቀይ ባህር ማዶ~እሺ ሰው ሰመጠ
በሳውዲ አደባባይ~አንገት ተቆረጠ
በሰሜን ደቡብ~እልፍ ሰው ታሰረ
መሪና ተመሪ~ሁሉም አመረረ፤
አምሳ ተገደለ
እቤት ተቃጠለ"
.
.
ነው መሪ ዜናችን~ አገር ቤት ከማዶ
ሰላም ማውራት ቀረ~ሁሌ ጥቁር መርዶ፤

Monday, July 18, 2016

"ወረድን......."

ቁልቁል ተራመድን~ከስልጣኔ ጓዳ 
ተራራውን ለቀን~ወረድን ወደ ሜዳ፤
ወረድን እምነት
ወደ 'ሸት ማንነት 
ወጣን ሰውነት

.....

.........

..............
......

.......

............

..................
.....
አንድ ሁለት እያልን

Wednesday, June 15, 2016

“I have a dream”

 I look in to the sun
And look in to the moon
All shines equally for the world
Why dark for African child?

I know my color is black
But we are equal at the dark
My flesh and blood
It is like what you had

Don’t hold my dignity
Make me free to fly on liberty
Give me full freedom
To fly on the field of wisdom

‹‹‹‹አዎ መምህር ነኝ!….›››

የትውልዱን ነገ ያዘልሁኝ ጀርባ
መጪውን እያሰብሁ ህልም የምባባ
አዎ መምህር ነኝ የእውቀት ደብተራ
ፈጣሪ በታች ሰውን የምሰራ

ጠመኔ ብናኝ በላጠው መዳፌ
መለፍልፍ ብዛት ደረቀ አፌ
ሰው ሃብታም የማደርግ ድህነት ታቅፌ
አዎ መምህር ነኝ
የእውቀት ደብተር እንጂ የባንክ ቡክ የሌለኝ

እንደ ደረሰች ሴት እውቀትን እያማጥሁ
ጠመኔ ታቅፌ ትውልድ ፊት የቆምሁ
ነገን እንዲሸከም ጮሄ የምሞግት
ደሞዝ ቀን የራቀኝ እንደ ዳግም ምፃት
አዎ መምህር ነኝ!
የመቶ ብር ምስል የሚያስደነግጠኝ