Saturday, August 18, 2018

‹‹የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት›› የአገው ህዝብ ወይስ የፖለቲካ ቁማርተኞች ጥያቄ?


                         (ሳይቃጠል በቅጠል፤ በዘላለም ጥላሁን) Must read!
እስኪ ልጻፍ፡፡ ዛሬ ካልጻፍሁ መቼ ልፅፍ ነው፡፡ እናቴ ጓዳውን፣ አባቴ ጋጣውን ተከፋፍለው እስኪለያዩ መጠበቅ የለብኝም፡፡ ምን ማለት እንደፈለግሁ አዊ ዞን የሚኖሩ ወጣቶች ይረዱኛል፡፡ ወደ ዋናው ነጥብ ከመግባቴ በፊት አንዴ ጠብቁኝ ‹‹የዘር ፖለቲካን ሰፈር ድረስ የዘራውን ሰው ሁሉ ልራገም››….‹‹ልጅ አይውጣላችሁ!›› ጨርሻለሁ!.....

እኔ ግን ይች ሀገር ታሳዝነኛለች፡፡ እንደ ዶሮ ብልት ተከፋፍላ ተከፋፍላ ማለቋ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ዛሬ ማንሳት የፈለግሁት ‹‹ጉዳዩ እየገፋ ስለመጣና የእዚህ ጉዳይ አራማጆች ዛሬ አዲስ አበባ ‹‹ራስ አምባ ሆቴል ›› ሲመክሩ ስለዋሉ ነው››

አሁን ‹‹አገው ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት›› የሚሆነው በየት በኩል ነው?……..ይህን ስል የአገውን ማህበረሰብ ማንነት ማሳነሴ አይደለም፡፡ ራሴን ማሳነስ ስለሚሆን፡፡ ሃቁ የአገው ህዝብ የራሱ ቋንቋ አለው፡፡ አብሮት ከሚኖረው አገውኛ ከማይናገረው ህዝብ የተለዬ ባህል እና ትውፊት ግን የለውም፡፡ ለጊዜው ትኩረቴን ‹‹የአዊ ዞን ህዝብ›› ላይ ላደርግ፡፡ ተከተሉኝ፡፡ ወደ ጉዳዩ ለመንደርደሪያ እንዲሆን እና ምሁራን ጉዳዩን በትኩረት እንዲያዩት ፍንጭ ለመስጠት ያህል እንዳንድ አሃዛዊ መረጃዎችን ማየቱ ጠቃሚ ነው፡፡

Thursday, August 16, 2018

የአዊ (አገው ምድር) የፈረስ ጉግስ ባህል

70 ዓመታት በላይ የሆነው ‹‹አዊ የፈረስ ማህበር›› ባህሉን ጠብቆ በማቆየቱ ‹‹ቅርስና ባህል ዘርፍ›› ለዘንድሮው በጎ ሰው ሽልማትከተመረጡ ሶስት ዕጩዎች አንዱ ሁኗል፡፡ የፈረስ ጉግስ ባህሉ ዝም ብሎ ለመዝናኛ የሚሆን ብቻ አይደለም፡፡ የማህበራዊ ስነ-ሰብ አጥኝዎች በአግባቡ ባያጠኑትም ቅሉ፣ የራሱ ታሪካዊ አመጣጥ አለው፡፡ ከታሪካዊ እውነታዎች እና አሁን የፈረስ ጉግስ ከሚዘወተርባቸው ሁነቶች ተነስቶ ሶስት መላምቶችን መገመት ይቻላል፡፡
1) አንደኛው ከመከረኛው ጦርነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡
መኪና፣ አውሮፕላን እና ዘመናዊ የጦር መሳሪያ በሌለበት ዘመን አብዛኛው የእርስ በርስም ሆነ ከውጭ ጠላት ጋር ይደረጉ የነበሩ ውጊያዎች የሚከወኑት በጦር እና ጎራዴ በሚደረግ የጨበጣ ውጊያ ነው፡፡ የጨበጣ ውጊያን በድል ለማጠናቀቅ ደግሞ ፈረስ ትልቅ አስተዋፅኦ ነበረው፡፡ የአድዋ ጦርነት በፈረስ አጋዥነት ለድል እንደበቃ ብዙ ማሳያዎች አሉ፡፡ ‹‹ባንዳ እርግማን›› አፋችን የሾለውን ያህል ‹‹ፈረሶችን›› አመስግነናቸው አናውቅም፡፡ ለኢትዮጵያ ነፃነት ‹‹ባንዳዎች›› እና ‹‹ከፈሪዎች›› ይልቅ ፈረስ የነበረው አስተዋፅኦ ታላቅ ነው፡፡ ፈረስ ለቀደሙ ነገስታት ባለውለታ፣ የህይወታቸው አለኝታ ነበር፡፡ ለዚህም ይመስላል ብዙ ነገስታት አባታቸው ይልቅ የፈረሳቸው ስም ጎልቶ የሚወጣው፡፡ ለምሳሌ የአፄ ቴወድሮስን ብናነሳ፡
‹‹ታጠቅ ብሎ ፈረስ፣ ካሳ ብሎ ስም
አርብ አርብ ይሸበራል፣ ኢየሩሳሌም››……ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፡፡

ከነፃው ፕሬስ ፋና-ዎጊዎች


(በቅዱስ ሃብት በላቸው)
ነሃሴ 9 ቀን በኢትዮጵያ የነፃ ፕሬስ ታሪክ ፋና-ወጊ ተብለው በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የሆነው የመብሩክ/መብረቅ ጋዜጣ አሳታሚና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ወርቁ ዓለማየሁ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየበት ዕለት ነው።ትንሿ ትግራይ!” በሚል ርዕስ በአንድ መንግስታዊ ተቋም ውስጥ ከላይ እስከታች የተሰገሰጉትን የአንድ ብሔር ሰዎች በማስረጃ ማጋለጡን ተከትሎ ድንገት ታፍኖ እስር ቤት ተጥሎ የነበረው ጋዜጠኛ ወርቁ፣ ከእስር ቤት እንደወጣ ነበር እስከወዲያኛው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን።