Showing posts with label ማህበራዊ ጉዳይ (Social Affair). Show all posts
Showing posts with label ማህበራዊ ጉዳይ (Social Affair). Show all posts

Saturday, May 18, 2019

ፓስተር፣ወታደርና ዶክተር

ሙጋቤ በአንድ ወቅት እንዲህ አሉ አሉ፡፡ 
ባይሉም እኔአልሁ፡፡ሃቁ ደረቅ ሃቅ ስለሆነ፡፡ የአፍሪካን ተማሪዎች በአራት ካታጎሪ ከፈሏቸው፡፡ ምን ብለው?
1)የአፍሪካ በጣም ጎበዝ ተማሪዎች ሕክምናና ምህንድስና ያጠናሉ፡፡ ሲመረቁም ህዝብ ያክማሉ፣ ሀገርና ከተማ ይገነባሉ፡፡
2)ደከም ያሉት ደግሞ ማህበራዊ ሳይንስ ያጠኑና የፖለቲካዊን መንበር ተቆጣጥረው የህክምና ባለሙያዎችንና መሃንዲሶችን ይመራሉ፡፡ 
3)ውጤት አልሳካ ብሏቸው ኮሌጅ ያልገቡት ደግሞ ፖሊስና መከላከያ ይሆኑና የፖለቲካውን መንበር የተቆጣጠሩ የማህበራዊ ሳይንስ ምሩቃንን አዙረው ይመራሉ፡፡ ሲነሽጣቸው አፈሙዝ አዙረው መንበሩ ላይ ይሰየማሉ፡፡ 
4)ትምህርት አልገባ ብሏቸው፣ ከትምህርት ቤት የተሰናበቱ ተማሪዎች ደግሞ ‹‹ፓስተር›› ይሆኑና የሕክምናውን ስራ ገድል ይከቱታል›› ብለዋል አሉ፡፡ ሐሳዊ ጋዜጠኞችንና አርቲስቶችን ከየት እንደመደቧቸው ግን አልተናገሩም፡፡ ነፍጥ አልያዙም እንጂ መደባቸው ከሶስተኛው ዲቢዚዎን አይዘልም፡፡

Thursday, November 1, 2018

‹‹ኧረ በህግ አምላክ…››



የልጅነቴ ስነ-ልቦና እና አሁን ያለንበት ሁኔታ ሁሌም ይጋጭብኛል፡፡ በልጅነቴ፣ ሰዎች ሌባን ወይም ጉልበተኛን ‹‹ኧረ በህግ አምላክ…›› ሲሉት ይቆማል፡፡ የዘረረውን በትር ወይም መሳሪያ ወደ ሰገባው ይመልሳል፡፡ ሌባውም ‹‹ኧረ በህግ አምላክ ቁም…› ሲባል ቀጥ ብሎ ይቆማል፡፡ ይህ የሚያሳየው ኢትዮጵያ ህገ-ሰብዕን ከህገ ህሊና ጋር አስተሳስራ ትኖር የነበረች ሀገር እንደሆነች ማሳያ ነው፡፡ ላለፉት ብዙ አስርት ዓመታት የሰማናቸውና ያየናቸው ‹‹አባቱ ዳኛ፣ ልጁ ቀማኛ›› አይነት ልሙጥ የሆነ የፍትህ ስርዓት ሂደት ሁላችንም ተስፋ ቆራጭ አድርጎናል፡፡ ‹‹ስልጣን እና ገንዘብ›› ኤልሻዳዮች ሁነው፤ ህግ ሲጣስ፣ ዳሃ ሲያለቅስ ማየት ብርቅ አይደለም፡፡ ፍትህ እውነትን የማስከበር ሂደት ነው፡፡ እውነት ደግሞ በአደባባይ ተረግጣ ነበር፡፡ በፍትህ ስርዓቱ ተስፋም ሆነ እምነት ካልነበራቸው ሰዎች አንዱ ነኝ፡፡  ይህን ስሜቴንም የዛሬ ሶስት ዓመት፣ ልክ በዚህ ወር ‹‹እውነትን ሰቀሏት›› በሚል አርዕስት የሚከተለውን ግጥም ከአባሪ የምስል ቅንብር ጋር በገፄ ለጥፌ ነበር፡፡

Wednesday, September 12, 2018

ሀሳብና ሰብዕና ቢለያዩስ?


/ መስፍን ወልደማሪያም ለኢትዮጵያ ውለታ ከዋሉ አንጋፋ ምሁራን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ከአፄው እስከ አሁኑ ስርዓት ድረስ የታሪክ ማጣቀሻ ሆነው በህይወት ካሉ ምሁራን ውስጥ አንዱ እኒህ ጎምቱ የታሪክ ምሁር ናቸው፡፡ 1960ዎች ኢትዮጵያ በረሃብ አለንጋ ስትገረፍ ከፕ/ ጌታቸው ኃይሌ እና መሰል የወገን ተቆርቋሪዎች ጋር በመሆን ታላቅ ውለታ ውለዋል፡፡ እኒህ ምሁር ‹‹አማራ የሚባል ብሔር/ ነገድ የለም›› በሚል አቋማቸው አማራ ነህ ተብሎ እንደ ኑግ በየቦታው እየተሰለቀ በነበረው ወጣት ዘንድ ትልቅ ተቃውሞ ሲሰነዘርባቸው እንደቆዬ ሁላችንም የምናውቀው ነው፡፡ የአሁኑ ዘመን ትውልድ ከእሳቸው አቋም ጋር መስማማት ቢሳነው በማንም መፍረድ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም በእሳቸው ትርክት እና በእኛ ትርክት መካከል ትልቅ የታሪክ መጋረጃ አለ፡፡ የታሪክ መጋረጃው ደግሞ ሰው በሰውነቱ ሳይሆን የደምና የአጥንቱን መሰረት ተከትሎ በዘውጌ ፖለቲካ እንዲተሳሰር ተደርጎ የተዘጋጀ መጥፎ መጋረጃ ነው፡፡ / መስፍን በሀሳባቸው ልክ ሆኑም አልሆኑም፣ ሰብዕናቸው መከበር አለበት፡፡ 

Monday, September 10, 2018

‹‹በደሃ እናቶች እምባና በወጣቶች ደም-የስልጣን ቁማር መጫወት ይብቃ!››

(የአዲስ ዓመት መልዕክት)
 
የፕ/ ብርሃኑ እናት ልጃቸውን ቦሌ ተቀብለው ለመሳም ታደሉ፣ የሌሎችም እንዲሁ፡፡ ያም ሆኖ ግን ስስታቸውን ምስሉ ይገልፀዋል፡፡ እናት ምንም ቢሆን እናት ናት፡፡ ለሴኮንድም የልጇን መከራ መስማት አትፈልግም፡፡ ከጀርባ ግን ታላቅ የእምባ ጎርፍ ይታየኛል፡፡ ልጆቻቸውን በአደባባይ በአገዛዙ በግፍ የተነጠቁ እናቶች፣ መሰል ምስሎችን ሲያዩ የሚያነቡት እምባ!  ከአንጀት ተንሰቅስቆ የሚወርድ ትኩስ አምባ! በበቃሽ የማይቆም እምባ!

Saturday, August 18, 2018

‹‹የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት›› የአገው ህዝብ ወይስ የፖለቲካ ቁማርተኞች ጥያቄ?


                         (ሳይቃጠል በቅጠል፤ በዘላለም ጥላሁን) Must read!
እስኪ ልጻፍ፡፡ ዛሬ ካልጻፍሁ መቼ ልፅፍ ነው፡፡ እናቴ ጓዳውን፣ አባቴ ጋጣውን ተከፋፍለው እስኪለያዩ መጠበቅ የለብኝም፡፡ ምን ማለት እንደፈለግሁ አዊ ዞን የሚኖሩ ወጣቶች ይረዱኛል፡፡ ወደ ዋናው ነጥብ ከመግባቴ በፊት አንዴ ጠብቁኝ ‹‹የዘር ፖለቲካን ሰፈር ድረስ የዘራውን ሰው ሁሉ ልራገም››….‹‹ልጅ አይውጣላችሁ!›› ጨርሻለሁ!.....

እኔ ግን ይች ሀገር ታሳዝነኛለች፡፡ እንደ ዶሮ ብልት ተከፋፍላ ተከፋፍላ ማለቋ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ዛሬ ማንሳት የፈለግሁት ‹‹ጉዳዩ እየገፋ ስለመጣና የእዚህ ጉዳይ አራማጆች ዛሬ አዲስ አበባ ‹‹ራስ አምባ ሆቴል ›› ሲመክሩ ስለዋሉ ነው››

አሁን ‹‹አገው ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት›› የሚሆነው በየት በኩል ነው?……..ይህን ስል የአገውን ማህበረሰብ ማንነት ማሳነሴ አይደለም፡፡ ራሴን ማሳነስ ስለሚሆን፡፡ ሃቁ የአገው ህዝብ የራሱ ቋንቋ አለው፡፡ አብሮት ከሚኖረው አገውኛ ከማይናገረው ህዝብ የተለዬ ባህል እና ትውፊት ግን የለውም፡፡ ለጊዜው ትኩረቴን ‹‹የአዊ ዞን ህዝብ›› ላይ ላደርግ፡፡ ተከተሉኝ፡፡ ወደ ጉዳዩ ለመንደርደሪያ እንዲሆን እና ምሁራን ጉዳዩን በትኩረት እንዲያዩት ፍንጭ ለመስጠት ያህል እንዳንድ አሃዛዊ መረጃዎችን ማየቱ ጠቃሚ ነው፡፡