Saturday, May 18, 2019

ፓስተር፣ወታደርና ዶክተር

ሙጋቤ በአንድ ወቅት እንዲህ አሉ አሉ፡፡ 
ባይሉም እኔአልሁ፡፡ሃቁ ደረቅ ሃቅ ስለሆነ፡፡ የአፍሪካን ተማሪዎች በአራት ካታጎሪ ከፈሏቸው፡፡ ምን ብለው?
1)የአፍሪካ በጣም ጎበዝ ተማሪዎች ሕክምናና ምህንድስና ያጠናሉ፡፡ ሲመረቁም ህዝብ ያክማሉ፣ ሀገርና ከተማ ይገነባሉ፡፡
2)ደከም ያሉት ደግሞ ማህበራዊ ሳይንስ ያጠኑና የፖለቲካዊን መንበር ተቆጣጥረው የህክምና ባለሙያዎችንና መሃንዲሶችን ይመራሉ፡፡ 
3)ውጤት አልሳካ ብሏቸው ኮሌጅ ያልገቡት ደግሞ ፖሊስና መከላከያ ይሆኑና የፖለቲካውን መንበር የተቆጣጠሩ የማህበራዊ ሳይንስ ምሩቃንን አዙረው ይመራሉ፡፡ ሲነሽጣቸው አፈሙዝ አዙረው መንበሩ ላይ ይሰየማሉ፡፡ 
4)ትምህርት አልገባ ብሏቸው፣ ከትምህርት ቤት የተሰናበቱ ተማሪዎች ደግሞ ‹‹ፓስተር›› ይሆኑና የሕክምናውን ስራ ገድል ይከቱታል›› ብለዋል አሉ፡፡ ሐሳዊ ጋዜጠኞችንና አርቲስቶችን ከየት እንደመደቧቸው ግን አልተናገሩም፡፡ ነፍጥ አልያዙም እንጂ መደባቸው ከሶስተኛው ዲቢዚዎን አይዘልም፡፡