Tuesday, August 3, 2021

ላለማልቀስ መጨከን‼️

 ወቅቱ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ነው። ጃፓን ክፉኛ ተደቁሳለች። ምድር የሬሳ ማሳ ሆናለች። የአሜሪካው ፎቶግራፈር አንድ ህፃን ላይ ቀልቡ አረፈ። ቤተሰቦቹን ያጣ፣ የሞተ ታናሽ ወንድሙን በጀርባው ያዘለ ህፃን። ሐዘኑን በእልህ የዋጠ፣ ላልማልቀስ የጨከነ ህፃን።

ወንድሙን ሬሳ ወደሚቃጠልበት ቦታ ይዞ ሄደ። የሚያቀጥለው ሰው "አምጣ የተሸከምኸውን ነገር ልቀበልህ" አለው።

ህፃኑም በንዴት "የተሸከምሁት ወንድሜን እንጂ ዕቃ አይደለም" አለው። ጨክኖ ከወንድሙ መለዬት አልቻለም። ነገር ግን ማልቀስ አልፈለገም። ከንፈሮቹን ነክሶ ሳጉን ወደ ውስጥ ሞጅሮታል። ይህ ምስል ዛሬ ድረስ በጃፓን እንደ ትልቅ የጥንካሬ ማሳያ ይቆጠራል። ጃፓን ከዚያ በኋላ ላለማልቀስ ወሰነች። እነሆ ላለፉት 80 ዓመታት ጃፓን አላለቀሰችም።

ኢትዮጵያ ሀገሬ መሰል አደጋ ፊቷ ላይ አንዣቧል። ከጦርነቱ ማግስት የሚኖረው የሞራል ስብራት ከባድ ነው። እልፎች ወላጆችን፣ ወንድምን፣ እህትን፣ ልጅን፣ ህፃናትን ያጣሉ።ትንቢት ሳይሆን እውነት ነው። ዛሬም በየቀኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖች እንደ ሸክላ እየደቀቁ ነው። ነገ የባሰ ያስፈራል። ኢትዮጵያ በየ20 እና 30 ዓመታት ጉዞ፣ ወጣቶቿን እንደ ራባት ድመት ቀርጥፋ የምትበላ ምታተኛ ምድር ናት። መድኃኒት ያጣች የደም ምድር-አኬልዳማ።

መፍትሔው አንድ ነው። ላለማልቀስ መጨከን ነው። ለዚህ ያበቁን ለመሳቅ ሲከጅሉ፣ እኛ ላለማልቀስ መጨከን። ላለማልቀስ ካልተጨከነ፣ ከጦርነቱ ማግስት ያለው የስነልቦና ቀውስ ሌላ ጦርነት ነው። ሌላ የሀገር ስብራት ነው። ዛሬ በስሜት ፈረስ ላይ ሆነን አይታይም። ነገ ቆም ስንል፣ የሁላችንም ምስል የዚህ ህፃን ነው። ማዳን ባንችል፣ ላለማልቀስ እንጨክን-ኢትዮጵያ ትቀጥል ዘንድ🙏

©Zelalem Tilahun

♻️Telegram: https://t.me/ZelalemTilahun2011

♻️YOUTUBE: https://www.youtube.com/channel/UCuUyLFXfRQIqnR82iwa43bg

♻️Twitter: https://twitter.com/zelalem_tilahun?s=09

♻️Facebook: https://www.facebook.com/zelalem.tilahun.12

 

ፍቅር ያሸንፋል!!


(የቴዲ አፍሮ ንግግር)
በታሪካዊዋና በገናናው ጀግና በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የትውልድ ሃገር በሆነችው የጐንደር ከተማ በተዘጋጀው በዚህ የምረቃት መርሀ ግብር ላይ የታደማችሁ ጥሪ የተደረገላችሁ ክቡራን እንግዶች ክቡራትና ክቡራን በቅድሚያ የከበረ ሰላምታዬን እያቀረብኩ በተለይ በዛሬው እለት ከብዙ ድካምና ጥረት በኋላ ፍሬያችሁን ለማየት ለበቃችሁ ተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ የሚል መልክቴን ላስተላልፍ እወዳለሁ።
በመቀጠልም በሕይወት ዘመኔ ሁሉ ከጉኔ ሳይለየኝ ያለ መታከት የረዳኝ ቅዱስ እግዚአብሔርን በታላቅ ትህትና ለማመስገን እወዳለሁ።
እንዲሁም በተሰማራሁበት የኪነ ጥበብ ዘርፍ ይህ የክብር ሽልማት ይገባሃል ብሎ በዛሬው እለት በእናንተ ፊት እንድቆም ምክንያት ለሆነኝ ለአንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርስቲ ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በማስከተልም የሕይወት አጋሬ ለሆነችዉ ባለቤቴ አምለሰት ሙጬ እና ለወላጅ አባቴ አቶ ካሳሁን ግርማሞ እንዲሁም ለወላጅ እናቴ ለወ/ሮ ጥላዬ አራጌና ለመላው ኢትዮጵያዊ ወገኖቼ ከፍያለ የአክብሮት ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ።
ከእዚህ በማስከተልም በማስተላልፈው አጭር መልክት ንግግሬን እቋጫለው።
ሃገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ የገባችበት ከባድ አጣብቂኝና እጅግ ፈታኝ ሁኔታ በሁሉም ዘንድ የታወቀ ቢሆንም እንኳን ነገርግን እናት ከመጨረሻው አስጨናቂ ምጥ በኋላ አዲስ ልጇን አይታ እንደምትደሰተው ሁሉ ሃገራችንም ከገጠማትና ሊገጥማት ከሚችለው ማንኛውም ከባድ አደጋ በደል ወጥታ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት አሸናፊ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም።
ላለፉት ቀላል ለማይባሉ ዓመታት አገራችንን አስጨንቆ የያዛትና አሁንም ላለችበት ቀውስ የዳረጋት የጐሳ ፖለቲካ አሳብ እንደማንኛውም ፍልስፍናና ሀሳብ ተወልዶ አድጐ አርጅቶና በስብሶ ተፈጥሯዊ ሞቱን ሞቷል።
ስለዚህም ከዚህ በኋላ መላው የሃገራችን ህዝብ በተለይም በተለይም ወጣቶች በጎሳና በዘር እንዲሁም በሃይማኖት ልዩነት ሳትናወጡ ከመቼው ጊዜ በላይ በአንድነትና በፍፁም ኢትዮጵያዊ ብሔራዊ ስሜት በተጠንቀቅ ፀንታችሁ መቆም ያለባችሁ ወይም ያለብን መሆኑን በአፅኖት ለማሳሰብ እወዳለሁ።
እኛ የአዲስቷ የኢትዮጵያ ትንሣኤ የአባቶቻችን ልጆች ኃይላችን ጉልበታችን እና መመኪያችን ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ነው።
ራዕያችንም ፍቅር ሠላምና ፍትህ የሰፈነባት
ታላቅ እና ገናና አንዲት ኢትዮጵያን ማየት ነው።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
ፍቅር ያሸንፋል።

Monday, February 17, 2020

#ውሸታሙ_ዓብይ ወይስ #ተመስገን?

 ከሰኔ 15 ማግስት ጄኔራል አሳምነውን በተመለከተ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፍትህ መፅሔት አንድ ሐተታ ፅፎ ነበር።ቃል በቃል ባይሆንም እንዲህ ይላል ተመስገን " ዝዋይ ማረሚያ ቤት ጄ/አሳምነው ጋር አብረን አንድ ክፍል ነበርን። እኛ ካርታ ጨዋታ እናበዛ ነበር። እኔ ሌሊት ተነስቼ ሁሉ እንጫወት ብዬ እቀሰቅስ ነበር። ጄ.አሳምነው ግን ፕሮግራም አውጥቶ ሌሎችን መፅሐፍ ቅዱስ ያስጠና ነበር። በጣም ይፆም ነበር። ለእኔ አሳምነው ይህንን ድርጊት ያደርጋል ብዬ ለማመን ይከብደኛል" በማለት የራሱን ብያኔ ያስቀምጣል።
ቀጥሎም አሳምነው ከአብይ ጋር ስለ ነበረው ግንኙነት እንዲህ ሲል ያትታል። ጄኔራል አሳምነው እስር ቤት እያለን ስለ አብይ አውርቶኝ ነበር። ቃል በቃል ያለውንም እንዲህ ሲል ያስቀምጣል
"ወደ እስር ቤት ከመግባቴ በፊት ወዳጆች ነበርን። አንድ ቀን የእኔን መኖሪያ አብይ በጓደኝነት ሰበቭ መጥቶ ሰለላት። እኔ ወደ እስር ቤት ስገባ የእኔ መኖሪያ ቤት አብይ መኖር ጀመረ" በማለት እንዳጫወተው ይገልፃል።

Saturday, May 18, 2019

ፓስተር፣ወታደርና ዶክተር

ሙጋቤ በአንድ ወቅት እንዲህ አሉ አሉ፡፡ 
ባይሉም እኔአልሁ፡፡ሃቁ ደረቅ ሃቅ ስለሆነ፡፡ የአፍሪካን ተማሪዎች በአራት ካታጎሪ ከፈሏቸው፡፡ ምን ብለው?
1)የአፍሪካ በጣም ጎበዝ ተማሪዎች ሕክምናና ምህንድስና ያጠናሉ፡፡ ሲመረቁም ህዝብ ያክማሉ፣ ሀገርና ከተማ ይገነባሉ፡፡
2)ደከም ያሉት ደግሞ ማህበራዊ ሳይንስ ያጠኑና የፖለቲካዊን መንበር ተቆጣጥረው የህክምና ባለሙያዎችንና መሃንዲሶችን ይመራሉ፡፡ 
3)ውጤት አልሳካ ብሏቸው ኮሌጅ ያልገቡት ደግሞ ፖሊስና መከላከያ ይሆኑና የፖለቲካውን መንበር የተቆጣጠሩ የማህበራዊ ሳይንስ ምሩቃንን አዙረው ይመራሉ፡፡ ሲነሽጣቸው አፈሙዝ አዙረው መንበሩ ላይ ይሰየማሉ፡፡ 
4)ትምህርት አልገባ ብሏቸው፣ ከትምህርት ቤት የተሰናበቱ ተማሪዎች ደግሞ ‹‹ፓስተር›› ይሆኑና የሕክምናውን ስራ ገድል ይከቱታል›› ብለዋል አሉ፡፡ ሐሳዊ ጋዜጠኞችንና አርቲስቶችን ከየት እንደመደቧቸው ግን አልተናገሩም፡፡ ነፍጥ አልያዙም እንጂ መደባቸው ከሶስተኛው ዲቢዚዎን አይዘልም፡፡