Saturday, June 27, 2015

MADIBA_LONG WALK TO FREEDOM

 Click to get the book in PDF
Nelson Mandela (Madiba), one of the great democratic leaders in the world had said many things about his stay in Ethiopia. His started the appreciation with the black Ethiopian pilot:
We put down briefly in Khartoum, where we changed to an Ethiopian Airways flight to Addis. Here I experienced a rather strange sensation. As I was boarding the plane, I saw that the pilot was black. I had never seen a black pilot before, and the instant I did I had to quell my panic. How could a black man fly an airplane? But a moment later I caught myself: I had fallen into the apartheid mind-set, thinking Africans were inferior and that flying was a white man’s job. I sat back in my seat, and chided myself for such thoughts. Once we were in the air, I lost my nervousness and studied the geography of Ethiopia, thinking how guerrilla forces hid in these very forests to fight the Italian imperialists.”

Sunday, June 21, 2015

የአስመሳዮች ዘመን

                   አስመሳይ ካልሆንህ አታንበው? ከጀመርኸው ጨርሰው!
አንድ ታሪክ ልንገራችሁ፡፡ እውነተኛ ታሪክ፡፡ በአንድ ወቅት በሰሜን ኢትዮጵያ ከሚገኙ ገዳማት ወደ አንዱ ብቅ ብየ ነበር፡፡ አንድ አባት የማግኘት ዕድሉ ገጥሞኝ ነበር፡፡ አባ ገ/ሕይወት ይባላሉ፡፡ በመንፈስ የበቁ፣ ለፀሎት የነቁ አባት፡፡ አባ አንድ ታሪክ ነገሩኝ፡፡ መግቢያውን ላለማገመድ ወደ ታሪኩ ልጋባ፡፡ አባ እንዲህ ሲሉ ጀመሩ፡፡
“አንድ ደግ ገበሬ ነበረ፡፡ እንደ ደጉ አብርሃም እንግዳ ተቀባይ ነበር፡፡ እንግዳ ይቀበላል፣ ያበላል፣ ያጠጣል፣ ያሳድራል፣ መንገድ አሳይቶ ይሸኛል፡፡ አንድ ቀን ግን ያልተጠበቀ ነገር ገጠመው፡፡ እንደተለመደው ሶስት ወጣቶች ከሩቅ ሀገር እንደመጡ ለዚህ ደግ ገበሬ አስረድተው “ የእግዜር እንግዳ” ነን አሳድሩን ሲሉ ተማጠኑ፡፡ "  አባ ድምፃቸውን ጠራርገው ትረካቸውን ቀጠሉ፡፡

Sunday, June 14, 2015

ዳማካሴ

                 click here for PDF
የኢትዮጵያ የባህል ህክምና ታሪክ ሲነሳ በፈዋሽነቱና በተደራሽነቱ በቀዳሚነት ብቅ የሚለው ዳማካሴ ነው፡፡የኢትዮጵያውያን ፈውስ፣ የረጅም ዘመን የጤና ወዳጅ-ዳመካሴ፡፡ታሪክ ጠቅስን መረጃ ተንተርስን መናገር ባንችልም ኢትዮጵያ ውስጥ በባህል ህክምና ባለሙያዎች ለፈውስ ከተገኙት ቀዳሚ ቅጠሎች አንዱ ዳማካሴ መሆኑን መገመት አያዳግትም፡፡አንድ ሰው የህመም  ስሜት ሲሰማው የሰፈር አዛውንቶች የሚሰጡት የመጀመሪያው ምክር ዳማካሴ ውሰድበት ነው፡፡ በመሆኑም ዳማካሴ፤ ጤና አዳምን፣ ፌጦንና ነጭ ሽንኩርትን አስከትሎ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በፈዋሽነቱና በተደራሽነቱ በቀዳሚነት ይታወቃል፤ ምንም እንኳ የቅጠሉ ዝርያና አበቃቀል ከቦታ ቦታ ቢለያያም፡፡ ታላቁ ገጣሚና የወግ ቀማሪ በውቀቱ ስዩም “ኢትዮጵያዊ ነኝ” በተሰኘ ግጥሙ እንዲህ ሲል ተቀኝቷል፡፡
                                               ……………..                     
“ግትር ጠላቴን በአጭር አንካሴ
ራስ ምታቴን በዳማካሴ
ነቅዬ ምጥል
አገር በነገር የማብጠለጥል
ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡”
……………….
ዳማካሴ ከሌሎች የመድሀኒትነት ባህርይ ካላቸው ዕፅዋት ለየት ይላል፡፡ 

Sunday, June 7, 2015

›››የሐበሻ ጀብዶ›››የኢትዮጵያውን የነፃነት ተጋድሎ›››


                                        ለፒዲኤፍ ይህንን ይጫኑ
ኢትዮጵያዊ ነህ? ሐበሻ ነህ? ሐበሻ ከሆንክ መጀመሪያ የሐበሻ ጀብዶንና ቀይ አንበሳን አንብብ፡፡ የቅድመ አያትህ፣ የአያትህና የአባትህ ታሪክ ነው፡፡ ዘመን የማይሽረው የሀበሻ ወኔ፣ ችግር ማይበግረው ጀግንነት፣ ሀገር ወዳድነትና ዘላለማዊ የሆነ የወገን ፍቅር በቀይ ቀለም የተከተቡበት ድንቅ መፅሐፍ፡፡ ስለማንነትህና ስለ ዘርህ አትጨነቅ ብቻ ሀባሻ ሁን፡፡ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ ወላይታ፣ትግሬ የትኛውንም የኢትዮጵያ ዘር ብትሆንም ይህ ያንተ የሀበሻው ታሪክ ነው፡፡ ቅድመ አያትህ፣ አያትህ፣ አባትህ ወይም ከወገኖችህ አንዱ አድዋ ነበር፤ ማይጨው ነበር፣ አቢ አዲ ነበር፣ መቀሌ ነበር፣ ኮረም ነበር፣ ተከዜ በረሃ ነበር፤ ኢትዮጵያን ከጠላት ሊታደግና ያልተበረዘ ማንነት ሊያወርስህ፡፡ አንተ የነዚያ ጀግኖች ውጤት ነህ፡፡ አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ደማቸውን አፍሰው በከፈሉልህ መስዋትነት ቀና ብለህ የምትጓዝ ነፃ ትውልድ! አንበው ቢያንስ ማንነትህና ታሪክህ ነው! ማንነቱን በትክክል የተረዳና ታሪኩን የሚያውቅ ትውልድ ማንም በደነፋ ቁጥር አይበረግግም፤ ታሪክ ጠቅሶ መፅሐፍ አስደጉሶ ስለማንነቱ ይከራከራል እንጂ፡፡

የአሲምባ ፍቅር


ከውስጥ በገነፈለ ስሜት፣ በተመረጡ ውብ ቃላት፤ የተፃፈ ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ የፍቅርና የትግል ታሪክ፡፡ ባለታሪኩ እንዲህ ብሎ ይጀምራል፡

“ከልብ በመነጨ ፍቅርና ቁርጠኝነት በለጋ እድሜየ የጀመርኩት ጉዞ አቅጣጫውን የቀየረው ባላሰብኩት ሁኔታና ወቅት ነበረ፡፡ ማንኛውም ሰው በሁኔታዎች አስገዳጅነት ያላሰበበትንና አልሞ ያልመረጠውን ሕይወት እንደሚቀበል ሁሉ እኔም እጣ ፈንታዬን ከተቀበልኩና በመራኝ ጎዳና መንገድ ከጀመርኩ በርካታ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡