Sunday, August 23, 2015

አስገራሚዋ ብላቴና (The Miracle Teenager)

By: Remzi Akibaw
በምስሉ የምትመለከቷት አስገራሚዋ እንስት ስምረት ይታይህ ትባላለች፡፡ ቃለ ምልልስ ያደረገላት ረምዚ አክባው የተባለ የማህበራዊ ድህረገፅ ጓደኛዬ ነው፡፡ ቃለ ምልልሱ ከያዘው አጅግ አሳዛኝ፣ አስገራሚና አስተማሪ ታሪክ የተነሳ እሱን አስፈቅጀ በዚህ ገፅ ለጥፌዋለሁ፡፡ ረምዚ አክባውን በአንባቢያን ስም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡
                ቃለምልልሱ ይቀጥላል….. መልካ ንባብ!!!
«እሽ እህታችን በመጀመሪያ ስምሽን ብታስተዋውቂን?…»
«ስምረት ይታይህ እባላለሁ
«እስኪ ካለን ሰዓት አንፃር ያሉትን ነገሮች አሳጥረን እናውራናእንዴት ነው ስራ ? እንዴትስ ወደዚህ ስራ ልትገቢ ቻልሽ
«ስራ ጥሩ ነውከጥሩነቱ በላይ ደግሞ ፈታኝ ነው። ወደዚህ ስራ የገባሁት ያው እናቴ ከኔ ውጭ ልጅም ሆነ ቤተሰብ ስላልነበራት ማንም የሚረዳት የለምለዛ ነው!( ፈገግታ…)»
«
ማለት ከመቼ ጀምሮ ነው አንቺ የምታስተዳድሪያት ? ትምህርት አትማሪም ወይስ ?…»
«ትምህርት እንኳን እማር ነበር……… (ከትንሽ ዝምታ በኋላ…) አምና በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ አመት water engeneering ተማሪ ነበርኩያው እንዳልኩህ ከእናቴ ውጭ የሚረዳኝ ዘመድ ምናምን አልነበረኝም። እናቴም ከእድሜዋ ጋር ተያይዘው ለሚመጡ ድካምና በሽታዎች ስለተጋለጠች ይሄን ከማድረግ ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረኝም።»

Thursday, August 20, 2015

“5 ብር በዕለተ ደብረታቦር"

(ለግብርና መር ፖሊሲያችን)
አምስት ብር እንደኔ የሌላችሁ አምስት ጊዜ በከንፈራችሁ ታጨበጭባላችሁ፡፡ ለማንኛውም ተከተሉኝ፡፡ ማጣት አይኑ ይጥፋ (አይን ካለው ማለቴ ነው) ድህነት ገድል ይግባ፤ ኧረ እንጦሮጦስ ይግባ::
               “ካላጡ ካልተቸገሩ
               መኖር ማን ይጠላል በአገሩ…”
ማንአልቦሽ ዲቦ በተስረቀረቀ ድምፅ ከዘፈነቻቸውና በልጅነቴ ከሰማኋቸው ዘፍኖች አንዱ ነው፡፡ ዛሬ ብትኖር ብዙ ትመርቅልን ነበር፡፡ አፈሩን ገለባ ያድርግላት፡፡ አሜን በሉ፡፡ አውነት ነው፤ ድህነት ባይኖር፣ ረሃብ በር ባያንኳኳ ማን ቀዬውን ጥሎ ይሰደዳል፡፡ ያውም አርሶ ጎተራ ሙሉ፤ ነግዶ ኬሻ ሙሉ ያፈሰበትን ቀዬ፡፡ ያውም ሳይሰስት አገርና ወገን የቀለበበትን ቀዬ፡፡ ያውምባድማውን ያብላህ!” ተብሎ የተመረቀበትን ቀዬ፡፡ ዕለተ ረቡዕ ባዕለ ደብረታቦር፣ ነሐሴ 13 2007 . ከምሽቱ 1215 ብሔራዊ፡፡ ደግነት ፊታቸው ላይ የሚነበብባቸውና የደስደስ ያላቸው ሁለት ምስኪን ገበሬዎች ወደኔ ተጠጉ፡፡ ወንድም-ዓለም! የሚል ድምፅ ከአቀርቀርሁበት የሞባይል ሜዳ አባነነኝ፡፡

Monday, August 17, 2015

የ “7” አንድምታ

በአዕማደ ምስጢር በመፅሐፍ ትርጓሜ
በአቋቋም ሰዓታት በቅኔ ዝማሜ
የሰባትን ቁጥር ሚስጢሩን የሚያውቁ
ይተረጉሙታል ሊቅ እያጠየቁ፤
””””””””””””””””””””””
ለአገሬ ግን ቅኔው ክፉኛ ከበዳት
ይሄ ሰባት ቁጥር ደግሞ ደግሞ ጣላት
ወርቁን ከሰሙ ጋር መለየት አቃታት፤

Wednesday, August 12, 2015

ዘሬ ከወዴት ነው?

ተጠየቅ ፈጣሪ ዘሬ ከወዴት ነው?
ትውልድን እንደዚህ የከፈለው ማነው?
ብዬ አንድ ቀን ሌሊት ጌታየን ጠየቅሁኝ
ንዴቴን አብርዶ እንዲህ ሲል አስረዳኝ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እኔ በአምላክ ጥበብ አንድ አዳም ስፈጥር
ሰይጣን በጎን ገብቶ ከፈላችሁ በዘር
አለና በሀዘን ትርጉሙን ነገረኝ
ዳግም ሁለተኛ ጥያቄ  ጠየቅሁኝ

Sunday, August 9, 2015

""መቼ ትመጫለሽ ""


ከታች አምና በፊት-መጣሁ ብለሽ ነበር
በመምጣትሽ ዜና-መኳንንት ሲሸበር
አንችን ለመቀበል-ስንት ኮርማ ሲመተር
ቦግ ብለሽ ተሰወርሽ-እንደ ምሽት ጀምበር
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በመቅረትሽ ዜና -ብዙ አልደነገጥንም
ነገ አትመጣም ብለን -ተስፋም አልቆረጥንም
ያው እንደነገሩ -አዲስ ሠርግ ደግሰን
ያሉንን ፍየሎች- ጠቦቶችን አርደን
በተስፋ ስንጠብቅ-ዳግም ተዘጋጅተን
አምና መጣች ብለው-ማዶ ማዶ ስናይ
ብልጭ ብለሽ ጠፋሽ-እንደ ሐምሌ ፀሐይ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡

Friday, August 7, 2015

"ሀገር-ሰው"










እናቴ እናቴ
የእውቀት መሠረቴ
የማንነት ሚዛን መከታ ኩራቴ
"ሀገር ማለት ሰው ነው"
"ሰው ማለት ሀገር ነው"
ብለሽኝ ነበረ ......
ምነው በኔ ዘመን ቃልሽ ተሰበረ
"ሀገር" ማለት "ገንዘብ" ሆኖ ተቀየረ
///////////////////////////////////////////