Friday, March 31, 2017

(‹ያለመቻል ግጥም››)

ልፅፍልሽ ብዬ፡
እንደ ገዳም መናኝ ቀልቤን ስሰበስብ
ለ አንቺነትሽ ቅኔ ገላጭ ቃላት ሳስብ
እንደ ርደ-መሬት ትዘላለች ልቤ
ፅሞናዬ ጠፍቶ ይበተናል ቀልቤ
‹‹ ፈዝዤ እቀራለሁ››
ጎንበስ ብሎ መፃፍ ተስኖት ወገቤ

Sunday, March 19, 2017

ለ ዝሆኖች ሲባል…

እዚያ ማዶ
ሰማይ ተዋዶ
የታላቅነት ታሪክ..በታዛቢነት ቆሟል
ትናንት ነገ.. አፉን ከፍቶ ይናገራል!
.
ወዲ ማዶ፡
ትውልድ ግራ ተጋብቶ እግሩ ወደ መራው ያዘግማል
ትናንቱን እየሻረ ዛሬውን ያሞግሳል!
;
መሃል ባለው ገደል
አንዱ አንዱን ሲበድል፤

Tuesday, March 14, 2017

ብርሃን ሩጫ~በሚያልፍ ዘመን ላይ 
እንደ ገለባ እሳት~ ሚከስም ንዋይ
ስነ ሰብዕ በታች~ከማንነት ማዶ
ዛሬነት ግርዶሽ~ነጋችን ተጋርዶ 
ልክ እንደ ይሁዳ~ሰው ገንዘብን ወዶ
.
.
ገዳይ ከሟች ጋራ~ አንድ እያደረ
እንግዲህ ሰው ማመን~እንደ ዋዛ ቀረ
--------------0----------------
      (ዘላለም፡ 29-07-08)

Friday, March 3, 2017

♥ አድዋ ♥

ወይ አንቺ አድዋ! 
የጥቁር ህዝብ ትንሳኤዋ!
በኩረ ነፃነት ምሰሶዋ!
-------------
የደመና ጥግ~የሰማይ ክሳድ 
የሐበሻ ዘር~የወኔ ሞረድ
አፍሪካ ጭቁን~የነፃነት በር 
መክፈቻ ቁልፏ~ይቻላልድር
የማንዴላ ኃይል~የሉተር ህልም 
መነሻ ሃሳብ~ትንቢተ ዓለም
አድዋ አንቺ ነሽ!
የሐበሻ ዘር~በደም የፃፈሽ