Monday, July 18, 2016

"ወረድን......."

ቁልቁል ተራመድን~ከስልጣኔ ጓዳ 
ተራራውን ለቀን~ወረድን ወደ ሜዳ፤
ወረድን እምነት
ወደ 'ሸት ማንነት 
ወጣን ሰውነት

.....

.........

..............
......

.......

............

..................
.....
አንድ ሁለት እያልን

Thursday, July 14, 2016

‹‹‹የ ኤደንብራው የሞት ጠላት›››


መሆንህን ቢያውቀው መከታ ሀገር
ህሙማን መሲህ ምሰሶና ማገር
ሞትማ ጨክኖ አይወስድህም ነበር
      (ዘላለም፣ 2008 .ም )
አንድ ትልቅ ዋርካ በስሩ ብዙ ነፍሳትን አስጠልሎ እንደኖረ ማን አስተውሎት ያውቃል፡፡ በቅርንጫፉ ያፈራቸው ፍሬዎችስ ለሌላ ዋርካ መሰረት እንደሆኑ ማን ይክዳል፡፡
ኢትዮጵያ በየ  ምህዳሩ ብዙ ዋርካዎች ነበሯት፣ አሏትም፡፡ ከነዚህ ቀደምት ዋርካዎች አንዱ ሸገር ተወልዶ፣ በረሃዋ ገነት ድሬዳዋ አቡጊዳ የቆጠረው፣ በኋላም ከተፈሪ መኮነን /ቤት እሰከ ግብፁ ቪክቶሪያ ኮሌጅ ቀጥሎም እስከ ታላቁ የእንግሊዙ ኤደንብራ ዩኒቨርሲቲ ብቃቱን ያስመሰከረው የሞት ጠላት ነው፡፡
ህፃንነቱ እናቱንና አባቱን የነጠቀውን ሞት ለመታገል የሞት መግቢያ ቀዳዳዎችን በዘመኑ ከነበሩ የኤደንብራ ጠበብቶች ከአንዴም ሁለቴ ተመላልሶ አጥንቷል፡፡ ከዚያም 40 አመታት ያክል ወላጆቹን የነጠቀው መላከ ሞት ጋር ሲታገል፣ የሺዎችን ህይወት ሲቀጥል ኖረ፡፡