Tuesday, December 20, 2016

‹‹ትዝብት….›››

 ሂደትላይሂደት
ቆርጠን ስንቀጣጥል~ቃላትን በቃላት
በጨለማ ግርዶሽ~ ትናንት ከሰመ
ዛሬም   ጭቅጭቅ~አቁሞን ተመመ
ሂደትሽንገላ
ወደፊትመላ
ነገ ነገ~እቅድ ስናሰላ
በማስመሰልና ስንፍና ጋሻ~እየተደገፈ
ያልኖርንበትነገ~ሳናየው አለፈ
(ምንጭ፡ ከታዛቢው  ማስታወሻ)

Friday, December 16, 2016

‹‹የማታ የማታ...››

ኢንሴኔ ኢሴራ ተታኤ - ማናሆ ጣጊሳኖ
ሳይኖሩ አለሁ ማለት - ባዶነት ዘግኖ 

እንደ በሬ ማግሳት - ትንኝን ሳይሆኑ 
እኩይ ጊዜ ታቅሮ - መራቅ ዘመኑ
ራሱ አያውቅ ነዳይ -ሚል ተረት ታቅፎ
ራስነት በላይ፣ ሰውነት መንፈስ አእምሮዬ ገዝፎ
መሰሪ ገመድ፤ ህሊና ችንካር እጄ ተቆልፎ 
ነገ እያልሁኝ ኖሬ - ከንቱ ይሉኝታ 
ዛሬዬን ገድዬ፣ ነገ እለያለሁ የማታ የማታ
.........( ዘላለም ጥላሁን)...............

Wednesday, December 14, 2016

ለካስ እድሜ ማለት...

እንደ ኤሊ ጉዞ~እንዲህ እንደዋዛ
ሴኮንድ ተደማምሮ~ደቂቃ እየበዛ
የሰዓታት ውህደት~በቀናት ሲሰላ
ሳምንትና ወራት~አመት እየሞላ
ሰው የሚባል ፍጡር~ይኖራል በመላ
ሲደምር ሲቀንስ~ ቁጥር ሲጣላ


በትናንት ትውስታ~ከልጅነት ማዶ
ዛሬ ገፄን ሳየው~ እርጅና ተዋዶ
"ለካስ እድሜ ማለት~ጅረት ነው ፏፏቴ
ሽው ብሎ የሚሮጥ~አንዱ በአንዱ ኮቴ"
(Thank You My God)

Thursday, September 29, 2016

ሁሌ_ጥቁር_መርዶ...

" ቀይ ባህር ማዶ~እሺ ሰው ሰመጠ
በሳውዲ አደባባይ~አንገት ተቆረጠ
በሰሜን ደቡብ~እልፍ ሰው ታሰረ
መሪና ተመሪ~ሁሉም አመረረ፤
አምሳ ተገደለ
እቤት ተቃጠለ"
.
.
ነው መሪ ዜናችን~ አገር ቤት ከማዶ
ሰላም ማውራት ቀረ~ሁሌ ጥቁር መርዶ፤

"ትንሽ ስጋ ይዞ ወደ በሬ ጠጋ…"

                                           (የሌቦች ጥበብ)
የሆነ ቦታ ነኝ-ከ ኦሮሚያ ሰማይ ስር፡፡ ትዕቢት የሚባል ምግብ 1-5 ተደራጅተን እየበላን ነው፡፡ ……(ለምን ትዕቢት የሚል ስያሜ እንደተሰጠው ግን የሚያውቅ የለም……ምን አልባት ይህን ምግብ የፈለሰፈው “ትዕቢት” የሚባል ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ ምን አልባትም “ትእቢተኛ” ሰው ሊሆን ይችላል፡፡) ከመሃከላችን በቅርቡ የተሾመ የአንድ ትልቅ ተቋም ሀላፊ አለ፡፡ በተቋሙ ስለነበረው ስር የሰደደ የሙስና መረብ ማውራት ጀመረ፡፡ መረቡን ለመበጠስ እየሞከረ እንደሆነም ነገረን፡፡….ግን ብዙ ውሾች እየጮሁ እንዳስቸገሩትም ነገረን፡፡ …..የትኞቹ ውሾች? ለምን ጮሁ? ብለን ጠየቅነው፡፡
 “ነገር በምሳሌ ጠጅ በብርሌ”…… እንዲሉ በምሳሌ ሊያስረዳን…… “ነገሩ አንዲህ ነው” ሲል ጀመረ፡ 
 “……..አንድ የጥንት የበሬ ሌቦች ጥበብ አለ፡፡ ሌቦቹ በሌሊት ከመንጋው መሃል በሬዎችን ለይተው ለማውጣት ሲሄዱ ከ ቀራተኛው በ ከፋ መልኩ ፈተና የሚሆኑባቸው ውሾች ናቸው፡፡ ስለዚህ የእነሱን ጩኸትና ልፊያ ለማለፍ ሲሉ ትንሽ ቁርጥራጭ  ስጋ ለውሾች ይዘው ይሄዳሉ፡፡ መጮህ ሲጀምሩ ትንሽ ስጋ ጣል ያደርጉላቸዋል፡፡ አሁንም ሲጮሁ ትንሽ ስጋ ጣል ያደርጉላቸዋል፡፡ አንደኛው ሌባ ውሾችን ሲያታልል አንደኛው በሬውን ይፈታል፡፡ ውሾችም በተደጋጋሚ ቁርጥራጭ ስጋ የሰጣቸውን ሰው እየተላመዱ ይሄዱና መጮህ ያቆማሉ፡፡ በቁርጥራጭ ስጋ ልሳናቸው ተዘግቶ የ ጌታቸውን በሬ ከመንጋው ለይተው ይዘው ሲሄዱ ዝም ይላሉ፡፡ በትንሽ ስጋ ብዙ ስጋ የያዘውን በሬ አሳልፈው ይሰጣሉ፡፡ አንድ ቀን ጌታቸው ይህን በሬ አርዶ ከዚህ በላይ ስጋ እንደሚያበላቸው ለ አፍታ ማሰብ አይችሉም፡፡ ጊዜያዊ ጉምጅታው በ አደራነት የሚጠብቁትን ታላቁን በሬ አሳልፈው እንዲሰጡ ያርጋቸዋል፡፡ ከዚህም አልፎ ሌባውን እንደጌታቸው ይቀርቡታል፡፡ …..” ሲል አስረዳን፡፡

Monday, September 12, 2016

የ 2009_አብይ_መልዕክት

#በታደሰ_ቁጥር_የምንቀር_ከኋላው
       (
በውቀቱ ስዩም)
አንድ እግሬን 2008 ላይ ተክዬ፣ አንድ አግሬን ደግሞ ወደ 2009 ለማራመድ ድንበር ላይ ቆሜአለሁ፡፡ የዘመን ድንበር ላይ! ማቆም አይደለም አይን ጥቅሻ ማዘግየት የማንችለው የዘመን ድንበር ላይ! እንደ ዘንድሮ አዲስ ዓመት ግራ አጋብቶኝ አያውቅም፡፡
ይህን የምለው በዓሉ ድምቀት ሳይሆን ከልቤ ነው፡፡ ……..ሰው የተሻለ ነገር ሲናፍቅ አዲስ አመትን አይደለም ነገ መንጋት በጉጉት ይጠብቃል፡፡
.......
ልጅነቴ ዘመን መለወጫ ቀን የሚሰጠኝን አዲስ እጀጠባብ (ካሽመር ሙሉ ልብስ) በማሰብ የጳጉሜን ሌሊቶች ሙሉ እንቅልፍ አይወስደኝም ነበር፡፡ አሁን ግን በመኖር እንጂ ካሽመር የሚታለል ልብ የለኝም፡፡

Wednesday, August 31, 2016

"ሪፖርት ላይ ይፀድቃል..."

ደበበ ሰይፉ "መሣቅ እኮ ይቻላል...አለማልቀስ ነው ጭንቁ" እንዳለው አንዳንዴ "ለበጣም" ሆነ "ገበጣ" ሳቅን ውስጥ ገፍቶ ማውጣት ለጤና ጥሩ እንደሆነ አንዳንድ ስቀው የማያውቁ ሐኪሞች ይመክራሉ፡፡
እስኪ እኛም እንገልፍጥ፡
ከላይ ወደ አነሳሁት ርዕስ ጉዳይ ስመለስ..... ዛሬ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝን ቀልድ መሠል እውነት ጀባ ልበላችሁ፡፡
ልማታዊ የሆኑ ወጣቶች ለአረንጓዴ ልማት አብዮቱ ንቅናቄ ችግኝ እየተከሉ ነው ( አብዮት የምትለዋ ቃል ለዘብ ባለ ልማታዊ ቃና ትነበብልኝ)፡፡
...... ቃና ስል ምን ትዝ አለኝ መሠላችሁ፡፡ ሰሞኑን እንደፈረደብኝ የተከራየሁት ቤት ሊሸጥ ስለሆነ ቤት እየፈለግሁ ነው፡፡ ዛዲያ እላችሁ አንዲት ፅሁፍ ላይ "ሽማግሌ" በንግግር
ላይ ግን የኮረዳነት ስሜት የሚቃጣቸው ሰትዯ የቤቱን ዋጋ ከነገሩኝ በኋላ.....ምን ቢሉኝ ጥሩ ነው፡፡