Friday, November 20, 2015

UNDERSTANDING RISK & FINANCE

Let me greet you first with this Poem:
<<Risk @ Crazy Tomorrow>>
We are in the hands of disaster 
Tomorrow is crazy as ever
We are creating millions of sin
Full of problems up and down
Whatever comes whatever gone
                                                Drink the waste of life as you gain
                                                you can't go back once you are born!
                                                Thus go and forecast the risk
                                                To have a light in the dark
                         [Zelalem T; AU, Addis Ababa, Ethiopia; Nov 19, 2015]
The International conference on "Building financial resilience of African nations and communities to climate and disaster risks" started on Nov 17, 2015 and end up on Nov 20, 2015 at the AU headquarters.

Tuesday, November 17, 2015

ለምን አታገቢም? (ክፍል-03)

         

                                       …
ካለፈው የቀጠለ
ምንም እንኳ ስንኞቹን እግር በእግር ባላስታውሳቸውም፤ ከሚከተለው ግጥም ጋር ተመሳሳይ ፍሬ ሃሳብ ያለው ዘፈን ሰምቼ አውቃለሁ፡፡
አግቢ ይሻልሻል ቶሎ ተሞሸሪ
እህትሽ ስትዳር ቁመሽ እንዳትቀሪ
ሴቶች ለምን ቶሎ አያገቡም? ይህንን ጥያቄ ለመመለስ የግድ ሴት መሆን አያሻም፡፡ ካየነው፣ ከሰማነው፣ ከታዘብነው፣ ከተማርነውና ካነበብነው በማንኪያ እየጨለፍን ዘርፈ-ትንሽ የሆኑ ምክንያቶችን ከመጥቀስ ማን ይከለክለናል? ሴቶቹ ስለእኛ ለመፃፍ የኛ ፍቃድ ያስፈልግሃል ካላችሁ፤ በፌደራል ፖሊሳዊ ሰላምታ እጂ ነስቻለሁ (ፌደራል ሲነሳ እንዳትበረግጉ)፡፡ ተፈቅዷል….እሺ ልቀጥል!
ከጎኖችህ አጥንት ሔዋን ሳትፈጠር
አዳም ሆይ ህይወትህ ምን ይመስል ነበር?”

Thursday, November 5, 2015

ለምን አታገባም? (ክፍል-02)

እንደምን አላችሁ፡ እስኪ ወጋችንን እንጠርቅ፡፡ ወጋችንን ያቆምነው 45 ዓመቱ ጓደኛዬ ላይ ነው፡፡                                            ልቀጥል……

ምነው ጋሸ ነገር እምቢ አለህ እንዴ?
ኧረ!…..አንተ!……እሱማ…………ጥዋት ጥዋት የአባቴን ጎራዴ እየመሰለ እያስቸገረኝ ነውአለ ደስ በሚል ፈገግታ፡፡ ደሃ ፈገግ ሲል እንዴት ደስ ይላል መሰላችሁ፡፡
ቀላል አልሳቅሁም፡፡ ምንም እንኳጥዋት ጥዋትየሚሉት ቃላት ባይዋጡልኝም፤ ሌላ ጊዜስ ብዬ ለመጠየቅ ግን ድፍረቱን አጣሁ፡፡
ያም ሆነ ይህ ጎራዴ መምሰሉ የስሜት ይሁን የሽንት ባይታወቅም፤ የጓደኛዬ መልስ ወንዶቹ እስከ 45 ዓመት ድረስ ጥሩ ተስፋ እንዳላቸው የሚያበስር ነው፡፡
ታዲያ ለምን አታገባም፣ እንዴት ለአንተ የምትሆን ሴት ታጣለህ?
ኧረ እሱስ አላጣሁም፡ እኔ ምመጥናት ሴት አትገኝም ነው እንጂ?”
ምን ማለት ነው እሰኪ አብራራልኝ?