Sunday, December 24, 2017

አዲስ አበባ (በረራ)

እንዲህ ብሎ መጣፍ አሰኘኝ፡፡
የአዲስ አበባ ሰማይ ጎህ ሲቀድ፥ ካድሬም ቢሆን የሚያሳቅፈውን የታህሳስን ውርጭ እንደምንም ታግዬ ከምኝታዬ ታፋታሁ፡፡ፀጥ ባለው የአዲስ አበባ ሰማይ ስር፥ የሰንበት ቅዳሴ አድማሱን ተሻግሮ ከብርዱ ጋር የሚታገለውን የአማንያንን ልብ በሐሴት ይጠራል፡፡
"እምነ በሐ....ቅድስት ቤተክርስቲያን......አረፋቲሃ......"
;
ይቀጥላል፡፡
ከገደል ማሚቶው ቀጥሎ የሌላ ደብር ምስጋና የብርዱን ቆፈን እንደ ሰም ያቀልጣል፡፡ አማኒያን ነጠላቸውን መስቀለኛ አጣፍተው ውር ውር ይላሉ፡፡
አዲስ የሁላችንም ናት፡፡ የካድሬው፥ የወሬኛው፥ የሃብታሙ፥ የድሃው፥ የዘረኛው፥ የኢ-ዘረኛው፥ የለፍቶ አዳሪው፥ የአማኙ፥ የቀማኛው፥ የአሳሪው፥ የታሳሪው፥ የምሁሩ፥ የባዶ ጭንቅላቱ፥ የእግረኛው፥ የባለ ሐመሩ፥ የጦም አዳሪው፥ የሰክሮ አደሩ ከተማ ናት፡፡

Friday, December 8, 2017

የሰፊው ህዝብ ግጥሞች

አንቺን የለመዱ ብዙ ሰዎች ሳሉ
የቤቱ ሙሉ አዛዥ እንግዳ ነው አሉ
አንቺ አሽከር ነገርሽ ከኮሶ ባሰሳ
ያስቀምጠኝ ጀመር ሌሊት እያስነሳ
አዋዜው በዛና ምላሴን ተኮሰው
አነካክቶ መብላት፥ መች አውቅና እንደ ሰው
አየሁ አዝመራሽን አውሬ ሲጨርሰው
እንዲህ ሆነሽ ቀሪ፥ ይመስለዋል ለሰው
አጎንብሰሽ መሄድ አላውቅ ብዬ እንደ ሰው
እቀና ብዬ ነው ቤቴ የፈረሰው
እኔን ከፋኝ እንጂ ሀገሬን ምን ከፋው
ግራር አበቀለ ዝሆን የማይገፋው

እኔ ልኮራመት እኔ ከሰል ልምሰል
ስቀሽ አታስቂኝ የደላሽ ይመስል


ሌላ ጨምሩ እስኪ?