Tuesday, March 14, 2017

ብርሃን ሩጫ~በሚያልፍ ዘመን ላይ 
እንደ ገለባ እሳት~ ሚከስም ንዋይ
ስነ ሰብዕ በታች~ከማንነት ማዶ
ዛሬነት ግርዶሽ~ነጋችን ተጋርዶ 
ልክ እንደ ይሁዳ~ሰው ገንዘብን ወዶ
.
.
ገዳይ ከሟች ጋራ~ አንድ እያደረ
እንግዲህ ሰው ማመን~እንደ ዋዛ ቀረ
--------------0----------------
      (ዘላለም፡ 29-07-08)

No comments:

Post a Comment