Tuesday, December 25, 2012

ጌታ ሆይ ቅደመኝ



በአንድ በኩል ስሰፋ ሌላው ሲያፈስብኝ
ጥሬውን ስቆላ ብስሉ ሲያርብኝ
አንዱን አለፍኩት ስል ሌላው ሲያናቅፈኝ
ቀን በቁሜ ስቃዥ ሌሊት ሲያባንነኝ
አንድ ጊዜ ሲያስቀኝ ደሞም ሲያስልቅሰኝ
      ቀኜ ሲበረታ ግራዬ ሲደክም
      ራስ ፍልጠት ሲይዘኝ ጨጓራ ሲያገግም
      ምን ይሆን መፍትሔው ለዚህ ከንቱ አለም
      ጌታ ሆይ ቅደመኝ ሸክሙን አልቻልሁም

No comments:

Post a Comment