Friday, May 5, 2017

‹‹የ አርበኞቹ ልጆች….››


አያቶቻችን፤
በ ሀገር ፍቅር የሰከሩ
አንበሳ ያሰገሩ
ጥሊያንን የገሩ
ሰንደቋን አንግበው
ረሃብ መከራን ታግሰው
ስለ ወገን  የሞቱ~ድንበር ያስከበሩ
እውነትም ጀግኖች ነበሩ!
እውነትም ፃድቆች ነበሩ!
አባቶቻችን ፤
በ እንጥፍጣፊ ፍቅር
ተዋድቀዋል ለ ሀገር!

አልፎ አልፎ
ራስነት ገዝፎ
ልዩነት ሲዘሩ
አጭደው ሲከምሩ
ዘር እየቆጠሩ
ድንበር እያሰመሩ
እኛን ልጆችን አፈሩ!
እኛ ልጆች፡
የ ሀገር ፍቅር ጠፍቶ~ፍቅረ ንዋይ ነግሶ
በ ልዩነት የ እሾህ አጥር~ጥላቻ ተለብሶ
በ እኛነት መቃብር~እኔነት ሰልጥኖ
ውሸት ብርሃን ለብሳ~እውነቱ ተከድኖ
ልባችን ከ አያቶች
እግራችን ከ አባቶች
መሆን እየሻተ
መሰረቱ ጠፍቶት~ሰርክ እየዋተተ
እንደ ቻይና በራድ~በ ቶሎ የሚሞቅ
እንደ በጋ ቅጠል~በ ቶሎ የሚደቅ
ስስ ወኔ ታቅፈን
የ አርበኞቹ  ልጆች መባሉ ተረፈን!

No comments:

Post a Comment